المختصر في صفة العمرة وأحكامها

المختصر في صفة العمرة وأحكامها

የዑምራ አፈፃፀምና ህግጋት አጠር ያለ ማብራሪያ

Language: lang_am
Prepared by: የእስላማዊ አስተምህሮቶችን በተለያዩ ቋንቋዎች አገልግሎት ማህበር የዕውቀት ዘርፍ ኮሚቴ
Version: 3.0
Translations 56
Amharic Assamese Azerbaijani Bambara +52
Attachments 7
PDF
Audio
Video
+3

የዑምራ አፈፃፀምና ህግጋት አጠር ያለ ማብራሪያ

ምስጋና ሁሉ የአለማት ጌታ ለሆነው አላህ የተገባ ነው። የአላህ ሶላትና ሰላም በነብያችን ሙሐመድ፣ በቤተሰቦቻቸውና በባልደረቦቻቸው ላይ ሁሉ ይስፈን።

በመቀጠልም፦

ይህ መልዕክት የዑምራን አፈፃፀም፣ ህግጋትና ስነ ስርዓት አጠር ባለ መልኩ የሚያብራራ ነው። በዚህም አንድ ዑምራ አድራጊ በአብዛኛው የሚያስፈልገውን ለማብራራት ጥረት አድርገናል።

አላህን ለተከበረው ፊቱ ጥርት ተደርጎ የተዘጋጀ እንዲያደርግልንና ለመላው ሙስሊሙ ማህበረሰብ ጠቃሚ እንዲያደርግልን እንጠይቀዋለን።

የእስላማዊ አስተምህሮቶችን በተለያዩ ቋንቋዎች አገልግሎት ማህበር የዕውቀት ዘርፍ ኮሚቴ

መግቢያ

የመጀመሪያው: አምልኮ ተቀባይነት እንዲያገኝ መሟላት ያለባቸው ቅድመ መስፈርቶች:

ሁለት መስፈርቶች እስካልተሟሉ ድረስ አምልኮ አላህ ዘንድ ተቀባይነት አይኖረውም።

እነርሱም:-የመጀመሪያው: ኢኽላስ (ስራን ለአላህ ፍፁም ማድረግ): ይህም በስራው የአላህን ፊትና የመጪውን አለም ምንዳ ለማግኘት አስቦ መስራት ነው። የበላይ የሆነው አላህ እንዲህ ብሏል: "አላህን ሃይማኖትን ለእርሱ ብቻ አጥሪዎች፤ ቀጥተኞች ሆነው ሊግገዙት እንጂ ያልታዘዙ ሲሆኑ (ተለያዩ)" [1] [አል-በይናህ፡ 5] የቁርአን አንቀፁ ትርጓሜም: ወደርሱና ወደ አምልኮው በመዞር ከርሱ ውጪ ያሉ አካላትን እንዲተዉ እንጂ ሌላ አልታዘዙም ማለት ነው። ተፍሲር ሰዕዲይ (ገፅ 538)

ነቢዩም የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና እንዲህ ብለዋል:- "ሥራ የሚለካው በኒያ ብቻ ነው። ሁሉም ሰው (የሚያገኘው) የነየተውን ልክ ነው።" (2) ቡኻሪ በቁጥር (1) እና ሙስሊም በቁጥር (1907) ዘግበውታል።

ሁለተኛው: በንግግርም ይሁን በተግባር ስራችን ነቢዩን (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) የተከተለ መሆን አለበት። ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ ብለዋል: "በዚህ ጉዳያችን ከእርሱ ያልሆነን አዲስ መጤ ያመጣ ይዞት የመጣው መጤ ነገር ውድቅ ነው።" ሙስሊም (1718) ላይ ባሰፈሩት ዘገባቸው "በርሱ ላይ የኛ ትዕዛዝ የሌለበትን ነገር የሰራ ሰዉ ስራው ወደርሱ ተመላሽ ነዉ።" (3) ቡኻሪ በቁጥር (2697) እና ሙስሊም በቁጥር (1718) ዘግበውታል። (4) ሙስሊም በቁጥር (1718) ዘግበውታል።

***

ሁለተኛ: የዑምራን አፈፃፀምና ህግጋትን የመማር ብይን:

አላህን በየትኛውም አምልኮ ሊያመልክ የፈለገ ሰው ስራው ሱናውን የገጠመ እንዲሆንለት በጉዳዩ ላይ የነበረውን የነቢዩን (የአላህ ሶላትና ሰላም በርሳቸው ላይ ይስፈንና) መመሪያ ሊማር ይገባዋል። ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በርሳቸው ላይ ይስፈንና) ሰዎች የርሳቸውን መመሪያ እንዲከተሉና በርሳቸው መመሪያ እንዲመሩ ያነሳሱ ነበር። ከማሊክ ቢን ሑወይሪሥ (አላህ መልካም ስራውን ይውደድለትና) እንደተላለፈው እንዲህ አለ: የአላህ መልክተኛ (የአላህ ሶላትና ሰላም በርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ ብለዋል: "(አሰጋገዴን) ስሰግድ እንዳያችሁት አድርጋችሁ ስገዱ።" (5) ቡኻሪ በቁጥር (6008) ዘግበውታል።

ከጃቢር (አላህ መልካም ስራውን ይውደድለትና) እንደተላለፈው: እንዲህ አለ: "ነቢዩን (የአላህ ሶላትና ሰላም በርሳቸው ላይ ይስፈንና) የእርድ ቀን በግመላቸው ላይ ሆነው ጠጠር እየወረወሩ እንዲህ ሲሉ ተመለከትኳቸው "ምንአልባት ከዚህ ሐጄ በኋላ ሌላ ሐጅ ማድረግ መቻሌን አላውቅምና የሐጅና ዑምራ ተግባራችሁን ከኔ ውሰዱ።" (6) ሙስሊም በቁጥር (1297) ዘግበውታል።

***

ሶስተኛ: የዑምራ ትሩፋት:

ዑምራ ሁለት ትሩፋቶች አሉት: ጥቅል የሆነ እና ልዩ የሆነ

ጥቅል የሆነ ትሩፋቱ:

ከአቡ ሁረይራ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ ብለዋል: «የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና እንዲህ ብለዋል: (ከዑምራ እስከ ዑምራ በመካከላቸው የተሰሩትን ወንጀል ማስማሪያ ነው። ተቀባይነት ያለው ሐጅ ለርሱ ከጀነት ውጪ ምንም ምንዳ የለውም።) (7) ቡኻሪ በቁጥር (1773) እና ሙስሊም በቁጥር (1349) ዘግበውታል።

ከዐብደላህ ቢን መስዑድ -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድለላቸውና- እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: "የአላህ መልክተኛ (የአላህ ሶላትና ሰላም በርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ ብለዋል: (ሐጅና ዑምራን አከታትላችሁ አድርጉ። ወናፍ [2] የብረትን፣ የወርቅንና የብርን ቆሻሻ እንደሚያስወግደው እነርሱም ድህነትንና ወንጀልን ያስወግዳሉ። ተቀባይነት ላለው ሐጅ ከጀነት በቀር ሌላ ምንም ምንዳ የለውም።"» ብረት ቀጥቃጭና አቅላጭ ብረት የሚያዘጋጅበት እሳት ነው። አትተምሒድ የኢብኑ ዐብዱል በር (15/102) (9) ቲርሚዚይ በቁጥር (810)፣ ነሳኢይ በቁጥር (2631) ዘግበውታል።

ልዩ የሆነ ትሩፋቱ ደግሞ በረመዷን ውስጥ ከተደረገ ነው: ከኢብኑ ዓባስ (አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና) እንደተላለፈው: ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ ብለዋል: "በረመዷን ውስጥ የሚደረግ ዑምራ ከኔ ጋር እንደሚደረግ ሐጅ ይቆጠራል።" [3] ማለትም: በሌሎች ዘገባዎች እንደተዘገበው ከኔ ጋር ከሚደረግ ሐጅ ጋር እኩል ነው ማለት ነው።

***

የዑምራ አፈፃፀም

የመጀመሪያው: የመዋቂት (የኢሕራም ማድረጊያ ስፍራዎች) ህግጋት:

መዋቂት (የኢሕራም ማድረጊያ ስፍራዎች): ማለት ሐጅ ወይም ዑምራ ማድረግ የፈለገ ሰው ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በርሳቸው ላይ ይስፈንና) ኢሕራም እንዲደረግበት የወሰኗቸው ስፍራዎች ናቸው።

ከነዚህ ስፍራዎች መካከል በአንዱ በኩል ሐጅን ወይም ዑምራን ነይቶ የሚያልፍ ሰው ከዛ ስፍራ ኢሕራም ማድረግ ግዴታው ነው። ያለ ኢሕራምም ያንን ስፍራ ማለፍ አይፈቀድለትም።

ከነዚህ ኢሕራም ማድረጊያ ስፍራዎች ይልቅ ወደ መካ ቅርብ የሆነ ሰው የርሱ ኢሕራም ማድረጊያ ስፍራው (ሚቃቱ) ያለበት ስፍራ ነው። ካለበት ስፍራ ሆኖ ሐጅንም ይሁን ዑምራን ኢሕራም ያደርጋል።

የመካ ነዋሪዎችና ከመካ ኢሕራም የሚያደርጉ ሰዎች ለሐጅ ከሆነ ከዛው ከመካ ኢሕራም ያደርጋሉ። ዑምራህ ከሆነ ግን ከሐረም ውጪ ወደሚገኝ ወደ ተንዒምና የመሳሰሉት በመውጣት ኢሕራም ያደርጋሉ።

በአየር የሚሄድ የሆነ ሰው በራሪው ኢሕራም በማድረጊያ ስፍራው (ሚቃቱ) ትይዩ ሲሆን ኢሕራም ያደርጋል። የኢሕራም ማድረጊያ ስፍራውን (ሚቃቱን) ትይዩ ከመሆኑ በፊትም ለኢሕራም ይዘጋጃል። እንዲሁም የኢሕራም ልብስንም ይለብሳል። ልክ በራሪው ከኢሕራም ማድረጊያ ስፍራ (ከሚቃቱ) ትይዩ ሲሆን ወዲያው ኢሕራም ያደርጋል። ከበራሪው እስኪወርድ ድረስ ኢሕራሙን ማዘግየት አይፈቀድለትም። በራሪው ስለሚፈጥን ከኢሕራም ማድረጊያ ስፍራው ኢሕራም ሳያደርግ እንዳያልፍ ከሰጋ በራሪው ኢሕራም ማድረጊያ ስፍራውን ትይዩ ከመሆኑ በፊት ለጥንቃቄ ያህል ተልቢያውን (ለበይከ አልላሁመ ለበይክ) እያለ መጀመር ይችላል።

ሁለተኛ: የኢሕራም አፈፃፀምና ህግጋት:

ኢሕራም ማድረግ ለፈለገ ሰው ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መፈፀሙ የተደነገገ ነው:

ገላ መታጠብ: ይህም ለወንድም ይሁን ለሴት የወር አበባና የወሊድ ደም ላይ ላለች ሴት ሳይቀር አፅንዖት የተሰጠው ሱና ነው።

- ከዑድ ቅባት ወይም ከሌላ ካገኘው ጥሩ መአዛ ካለው ቅባት ጭንቅላቱንና ፂሙን መቀባት። የተቀባው ቅባት ወይም ሽቶ መአዛው ከኢሕራም በኋላ መቅራቱ ምንም ጉዳት የለውም። ሴት ከሆነች ግን ባዳ ወንዶች እንዳያሸቱት ሲባል ሽታ ያለውን ቅባት መቀባት አይፈቀድላትም።

- የኢሕራም ልብስ መልበስ: ይህም ሽርጥና ኩታ ነው። ሱናው ነጫጭና ንፁህ ወይም አዳዲስ መሆናቸው ነው። ሴት ልጅ ግን በጌጥ ያልተገላለጠች ሆና የፈለገችውን ልብስ ለብሳ ኢሕራም ታደርጋለች። ነገር ግን ኒቃብና ጓንት ከመልበስ ትቆጠባለች። ፊቷንና እጇንም ከነዚህ ውጪ ባለ ልብስ ትሸፍናለች።

ግዴታም ይሁን ወይም ሱና የተደነገገ ከሆነ ሶላት ከሰገዱ በኋላ ኢሕራም ማድረግ፤ ግዴታ ግን አይደለም።

(ለብበይከ አልላሁምመ ዑምራህ) ይላል። ለሌላ ሰው ከሆነ ዑምራ ያደረገው (ለብበይከ አልላሁመ ዑምረተን ዐን ፉላን) ይላል። ፉላን (እከሌ) በሚለው ፋንታ ዑምራ የሚያደርግለትን ሰው ስም ይተካበት።

ኢሕራም ማድረግ የፈለገ ሰው የሐጅ ወይም የዑምራ ስነ ስርዓቱን አሟልቶ ከመስራት የሚያደናቅፈኝ ነገር ይከሰታል ብሎ ከፈራ ኢሕራም ሲያደርግ (ለብበይከ አልላሁመ ዑምራህ፣ የሚያግደኝ ነገር ከተከሰተ የኢሕራሜ ፍፃሜ የታገድኩበት ቦታ ነው።) በማለት መስፈርት ማስቀመጥ ይፈቀድለታል። ኢሕራም ሲያደርግ ይህንን መስፈርት ካስቀመጠ በኋላ የሐጁን ወይም የዑምራውን ስነ ስርዓት ከመሙላት የሚያግድ ነገር ከተከሰተ በዛው ወቅት ከኢሕራሙ ይፈታል። ምንም የማድረግ ግዴታም አይኖርበትም።

ከዚያም ተልቢያ አብዝቶ ይበል: አባባሉም (ለበይከ አልላሁምመ ለበይከ፣ ለበይከ ላ ሸሪከ ለከ ለበይክ፣ ኢንነል ሐምደ ወንኒዕመተ ለከ ወልሙልክ ላ ሸሪከ ለክ) [4] ወንድ ከሆነ ተልቢያውን ሲል ድምፁን ከፍ ያደርጋል። ሴትም ብትሆን ባዳ ወንዶች ባሉበት ቦታ እስካልሆነች ድረስ ድምጿን ከፍ ታደርጋለች። ኢሕራም ላይ ያለ ሰው ተልቢያ ማብዛት ይገባዋል። በተለይ ሁኔታዎችና ወቅቶች ሲለዋወጡ ለምሳሌ ከፍታ ሲወጣ ወይም ቁልቁለት ሲወርድ ወይም ምሽት ወይም ንጋት ሲደርስ ተልቢያ አብዝቶ ይበል። ሰውዬው (ለብበይከ) ማለቱ ትርጉሙ: ጌታዬ ሆይ! ደግሜ ደጋግሜ ጥሪህን አቤት ብያለሁ። ሃሳቡም ሰውዬው የጌታውን ጥሪ ማክበሩንና ትእዛዙን ፈፃሚ መሆኑን እየገለፀ ነው። "ኢንነል ሐምደ ወንኒዕመተ ለከ ወልሙልክ" (ሐምድ) ማለት ተመስጋኙን ውዴታንና ልቅናን ባቀፈ ምሉዕ ባህሪያት ማውሳት ማለት ነው። ደጋግሞ ካመሰገነ ውዳሴ ይባላል። (ወንኒዕመተ) ማለት አላህ ባሮቹ ፍላጎታቸው እንዲሳካ እና የሚጎዳቸው እንዲወገድ ፀጋውን መዋሉ ነው። (አልሙልክ) ማለት ንግስናም ያንተ ነው። አላህ ተባረከ ወተዓላ ብቻ ነው ንጉሱ ማለት ነው። (ላ ሸሪከ ለክ) ማለት አላህ ብቸኛ በሆነበት ምሉዕ ባህሪያት አንድም የሚጋራው የለም ማለት ነው። አላህ ብቸኛ የሆነበት ሲባልም ለምሳሌ በንግስና፣ በመፍጠር፣ በማስተናበርና በተመላኪነት ያለውን ብቸኝነት ይጠቀሳሉ። ከመጅሙዕ ፈታዋና ረሳኢሉል ዑሠይሚን (22/96) አጠር ተደርጎ የቀረበ።

በዑምራ ወቅት ኢሕራም ካደረገበት ጊዜ ጀምሮ ጦዋፍ እስኪጀምር ድረስ ተልቢያ ማድረግ የተደነገገ ነው።

ኢሕራም ያደረገ ሰው አንድ ሙሕሪም ከኢሕራሙ እስኪፈታ ድረስ የሚከለከላቸው ነገሮችን ከመዳፈር መጠንቀቅ ግዴታው ነው።

ሶስተኛ: የጦዋፍ አፈፃፀም:

ኢሕራም ያደረገ ሰው መስጂደል ሐራም ሲገባ ቀኝ እግሩን ማስቀደሙ ሱና ነው። መስጂድ ሲገባ የሚባለውን ዱዓም ይበል። መስጂድ ሲገባ ከሚባሉ ዱዓዎች መካከል እጅግ የተረጋገጠው ዱዓ "አልላሁምመ-ፍተሕ ሊ አብዋበ ረሕመቲክ" ትርጉሙም "አላህ ሆይ! የእዝነት በርህን ክፈትልኝ" ማለት ነው። ይህን ዱዓ የሚለውም መስጂደል ሐራም ሲገባ ብቻ ሳይሆን ማንኛውም መስጂድ ሲገባ ነው።

ጠዋፍ መጀመር የፈለገ ጊዜ ተልቢያውን ያቋርጣል። "የኢድጢባዕ" አለባበስ ይለብሳል። አለባበሱም: የኩታውን መሃል ቀኝ ብብቱ ስር በመክተት የኩታውን ጫፍ በግራ ትከሻው ላይ ማድረግ ነው። ጦዋፍ አድርጎ እንደጨረሰም ኩታውን ከጦዋፍ በፊት ወደነበረበት አለባበስ ይመልሰዋል። የኢድጢባዕ አለባበስ የሚፈፀመው በጦዋፍ ወቅት ብቻ ስለሆነ ነው።

ቀጥሎ ወደ ሐጀረል አስወድ (ጥቁሩ ድንጋይ) ቀደም በማለት በቀኝ እጁ ጥቁሩን ድንጋይ በመዳበስ ይስመዋል፤ መሳሙ ካልገራለት በእጁ ይዳብስና እጁን ይሳም፤ ይህም ካልገራለት በእጁ ሰላም ይለዋል ወይም እንደ ዘንግና የመሳሰሉትን ነገር በመዳበስ ይስመዋል። ይህም ካልገራለት ወደ ሐጀረል አስወድ በመዞር እጁን ወደርሷ በመጠቆም እጁን ሳይስም ያልፋል። ምንም ሳይገፋፋ ሰዎችን ሳያውክና በሰዎች ሳይታወክ መፈፀም በላጭ ነው።

ሐጀረል አስወድን (ጥቁሩን ድንጋይ) ሲዳብስ ወይም ወደርሱ ሲጠቁም (አላሁ አክበር) ይበል።

ከዚያም ቀኝ አቅጣጫን በመያዝ በይተል ሐራምን በግራው በኩል ያደርጋል። ሩክነል የማኒ ጋር ሲደርስም ሳይስመው ይዳብሰዋል። ይህ ካልገራለት ምንም ሳይገፋፋም በእጁም ወደርሱ ሳይጠቁም ያልፋል።

በሩክነል የማኒ እና ሐጀረል አስወድ መካከል ሲደርስ (ረብበና አቲና ፊ ዱንያ ሐሰነተን ወፊልአኺረቲ ሐሰነተን ወቂና ዓዛበን-ናር) ይበል። ትርጉሙም (ጌታችን ሆይ! በምድረ አለም ደግን ነገር (ፀጋን) በመጨረሻይቱም አገር ደግን ነገር (ገነትን) ስጠን፤ የእሳትንም ቅጣት ጠብቀን።) ማለት ነው።

በሐጀረል አስወድ በኩል ባለፈ ቁጥር በእጁ ወደርሱ እየጠቆመ (አላሁ አክበር) ይበል።

በተቀሩት የጦዋፍ ዙሮች የፈለገውን ዚክር፣ ዱዓና ቁርአን ይበል።

ሱናው በሶስቱ የመጀመሪያ ዙሮች ሶምሶማ ማድረግ ነው። ሶምሶማ ማለት: እርምጃዎችን ከማቀራረብ ጋር ፈጠን ያለ አረማመድ መራመድ ነው። የተቀሩትን አራት ዙሮች ግን የተለመደውን እርምጃ እንጂ የሚራመደው ሶምሶማ አያደርግም።

ጦዋፉን አሟልቶ እንደጨረሰም ወደ መቃም ኢብራሂም በመሄድ ይህንን ይበል: (ወትተኺዙ ሚን መቃሚ ኢብራሂመ ሙሶላ) ትርጉሙም (ከኢብራሂምም መቆሚያ መስገጃን አድርጉ።) ማለት ነው። (አል‐በቀራህ: 125) ቀጥሎ ከገራለት ሁለት ረከዓን ከመቃሙ ኢብራሂም ኋላ ይሰግዳል። ካልገራለት ደግሞ መስጂዱ ውስጥ በሚገኝ ማንኛውም ስፍራ ይሰግዳል። በመጀመሪያው ረከዓ ከፋቲሓ በኋላ: (ቁል ያ አይዩሃል ካፊሩን) ይቀራል። [ሱረቱ አል-ካፊሩን:1] በሁለተኛው ረከዓ ከፋቲሓ በኋላ (ቁል ሁወሏሁ አሐድ) ይቀራል። [አልኢኽላስ:1]

አራተኛ: የሰዕይ (በሰፋና መርዋ መካከል የመሮጥ) አፈፃፀም:

ጠዋፍና ሁለቱን ረከዓዎች ባጠናቀቀ ጊዜ ወደ ሰዕይ ማድረጊያ ስፍራ ይወጣል። ወደ ሰፋ የቀረበ ጊዜም ይህንን ይበል: (ኢንነስ-ሰፋ ወልመርወተ ሚን ሸዓኢሪልሏህ) ትርጉሙም (ሰፋና መርዋ ከአላህ (ትእዛዝ መፈፀሚያ) ምልክቶች ናቸው።) ማለት ነው። (አልበቀራህ፡ 158) ከዚያም "አላህ ከጀመረበት እጀምራለሁ።" ይላል። ከዚያም "አብደኡ ቢማ በደአ'ላሁ ቢሂ" (ትርጉሙ፡ አላህ ከጀመረበት እጀምራለሁ።) [12] (12) ሙስሊም በቁጥር (1218) ዘግበውታል።

ቀጥሎ ካዕባን መመልከት እስኪችል ወይም ወደ ካዕባ አቅጣጫ ዞሮ ካዕባን እስከሚቅጣጭ ድረስ ወደ ሰፋ ይወጣል። አላህን በመነጠል ተክቢራ ይላል። (ላ ኢላሃ ኢለሏህ ወሕደሁ ላ ሸሪከ ለህ፤ ለሁል ሙልኩ ወለሁል ሐምዱ ወሁወ ዐላ ኩሊ ሸይኢን ቀዲር፤ ላ ኢላሃ ኢለሏሁ ወሕደህ፣ አንጀዘ ወዕደህ፣ ወነሰረ ዐብደህ፣ ወሀዘመል አሕዛበ ወሕደህ) የሚለውን ውዳሴ ሶስት ጊዜ ደጋግሞ ይበል። በየመሃሉም ዱዓ ያድርግ። (ላ ኢላሃ ኢለላህ ወሕደሁ ላ ሸሪከ ለህ፤ ለሁል ሙልኩ ወለሁል ሐምዱ ወሁወ ዐላ ኩሊ ሸይኢን ቀዲር፤ ላ ኢላሃ ኢለላሁ ወሕደህ፣ አንጀዘ ወዕደህ፣ ወነሶረ ዐብደህ፣ ወሀዘመል አሕዛበ ወሕደህ) (ትርጉሙም፡ ከአላህ በቀር በእውነት የሚመለክ አምላክ የለም፤ ለርሱም ተጋሪ የለውም፤ ንግሥናም የርሱ ብቻ ነው፤ ምስጋናም ለርሱ ብቻ የተገባው ነው፤ እርሱ በሁሉም ነገር ላይ ቻይ ነው፤ ከአላህ በቀር በእውነት የሚመለክ አምላክ የለም፤ ብቸኛ አምላክ ነው፤ ቃሉንም ፈፀመ፤ ባርያውንም ድልን አቀዳጀ፤ ብቻውን ሆኖ ስብስቦችን አሸነፈ።) ከዚያም በዚህ መካከል የቻለውን ያህል ዱዓእ ያደርጋል (አላህን ይማጸናል)። ይህንን ዚክር እና ዱዓእ ደግሞ ሶስት ጊዜ ደጋግሞ ይላል። [13] (13) ሙስሊም በቁጥር (1218) ዘግበውታል።

ቀጥሎ ከሶፋ ወደ መርዋ እየተራመደ ይወርዳል። አረንጓዴው ምልክት ዘንድ ሲደርስም በደንብ ይሮጣል። ሁለተኛው አረንጓዴ ምልክት ዘንድ ሲደርስ የተለመደውን እርምጃ ይራመድ። በደንብ መሮጥ ለሴት ልጅ አልተደነገገላትም።

መርዋ ዘንድ የደረሰ ጊዜ ሰፋ ላይ የፈፀመውን አምሳያ ማድረግ ተደንግጎለታል። (ቁጥር ሁለት ላይ ቀደም ብሎ የተጠቀሰውን)

ከዚያም ከመርዋ ወደ ሶፋ እየተራመደ ይውረድ። አረንጓዴው ምልክት ዘንድ የደረሰ ጊዜም በደንብ ይሮጥና ሁለተኛው አረንጓዴ ምልክት ዘንድ የደረሰ ጊዜ የተለመደውን እርምጃ ይራመዳል።

ሰባት ዙር እስኪሞላ ድረስም ልክ በዚሁ መልኩ ይፈፅማል። ከሶፋ ተነስቶ መርዋ እስኪደርስ ያለው ጉዞ አንድ ዙር ይባላል። ከመርዋ ወደ ሶፋ ሲመለስ ደግሞ ሁለተኛ ዙር ይባላል።

ሰዕይ በሚያደርግ (በሚሮጥበት) ጊዜ የፈለገውን ዚክር፣ ዱዓና ቁርአን ይበል።

አምስተኛ: ፀጉርን የመላጨት ወይም የማሳጠር አፈፃፀም

ዑምራ አድራጊው ጦዋፉንና መሮጡን እንዳሟላ ወንድ ከሆነ ጭንቅላቱን መላጨቱ ወይም ማሳጠሩ ግዴታ ነው። ሱናው መላ ጭንቅላትን መላጨት ወይም ማሳጠር ነው።

ዑምራው የተፈፀመው እስከ ሐጅ ባለው ጊዜ ድረስ የጭንቅላት ፀጉር ድጋሚ በማይበቅልበት ልክ በአጭር ወቅት ካልሆነ በቀር መላጨቱ ከማሳጠር በላጭ ነው። እንደዚያ ከሆነ ግን በማሳጠር ላይ ብቻ ይቆጠብ።

ዑምራ አድራጊዋ ሴት ከሆነች ከፀጉሯ ጫፍ የጣት ክፋይ ያህል ታሳጥር።

ኢሕራም ያደረገ ሰው የሚከለከላቸው ነገሮች

ኢሕራም ላይ ክልክል የሆኑ ነገሮች የሚከተሉት ናቸው

- ሰውነቱ ላይ የሚገኝን ማንኛውንም ፀጉር መላጨት ወይም ማሳጠር፤

- የእግርንም ይሁን የእጅ ጥፍርን ሙሉ ለሙሉም ይሁን የተወሰነውን መቁረጥ፤

- ከጭንቅላት ጋር የሚነካካ በሆነ ነገር ጭንቅላትን መሸፈን፤ ለምሳሌ: ኮፊያና ጥምጣም፣ ኩታን ወይም መሀረቡን ጭንቅላት ላይ ማድረግ ወይም ብርድልብስ ወይም ካርቶንና ከነዚህ ውጪም መሰል ነገሮችን ለጭንቅላት መሸፈኛ የሚታሰቡ ነገሮችን ጭንቅላት ላይ ማድረግ ነው። ይህ ክልከላ ግን ሴቶችን ሳይሆን ወንዶችን ብቻ ነው የሚመለከተው።

- የተለመደውን በሰውነት ልክ ተለክተው የሚዘጋጁ ልብሶችን በተለመደው መልኩ መልበስ ነው፤ ለምሳሌ ያህል ሙሉ የተሰፉ ልብሶች፣ ሱሪ፣ ጀለቢያ፣ ካልሲ፣ ጓንት ይጠቀሳሉ። ይህ ግን ሴቶችን ሳይሆን ወንዶችን ብቻ የሚመለከት ነው። ሴት ልጅ የምትከለከው:-

- ኒቃብ ወይም ማንኛውም ኒቃብን የመሰሉ ፊት መሸፈኛዎችን መልበስ ነው፤ ባዳ ወንዶች ፊት ከሆነች ግን መሸፈኛው ከፊቷ ጋር ቢነካካ እንኳ በተለመደው ፊት መሸፈኛ ፊቷን የመሸፈን ግዴታ አለባት። ፊቷን ስትሸፍን ከፊቷ ጋር እንዳይነካካ በሚል ጭንቅላት ማሰሪያ ወይም የመሳሰሉትን መጠቀም አይደነገግላትም። ይህ የተደነገገ መሆኑን የሚጠቁምም ምንም ማስረጃ የለምና።

- እጆቿ ላይ ጓንቶችን ማጥለቅም ትከለከላለች፤ ባዳ ወንዶች ፊት ግን እጆቿን ዓባያዋ ውስጥ በመክተት የመሸፈን ግዴታ አለባት።

- በተጨማሪ ኢሕራም ላይ ያለ ሰው ከሚከለከላቸው ነገሮች ሰውነቱን ወይም የኢሕራም ልብሱን ሽቶ መቀባት፤

- የየብስ እንስሶችን አድኖ መግደል ወይም ባይገድሉ እንኳን የማደን ሙከራ ማድረግ፤

- ለራሱም ይሁን ለሌላ ሰው ማጨት፤

- ኒካሕ ማሰር፤

- ከግንኙነት ውጪ ያለ የስሜት መነካካት ለምሳሌ መሳምና በስሜት መተሻሸት፤

- ግብረስጋ ግንኙነት ማድረግ፤

የዑምራ ተግባራት ማጠቃለያ (የመጽሐፉ ውጫዊ ልባጅ ላይ ወይም የመጨረሻው ገጽ ላይ ይሆናል)

- ገላ መታጠብ

- ሽቶ መቀባት

- የኢሕራም ልብስ መልበስ

- ኢሕራም እርሱም: ወደ ዑምራ ወይም ሐጅ ተግባር መግቢያ ኒያ ነው።

- ተልቢያ

- በአላህ ቤት ጠዋፍ ማድረግ

- ከመቃሙ ኢብራሂም ኋላ ሁለት ረከዓ መስገድ

- በሰፋና መርዋ መካከል መሮጥ

- መላጨት ወይም ማሳጠር አላህ የበለጠ ዐዋቂ ነው። የአሏህ ሰላትና ሰላም በነቢያችን ሙሐመድ ላይ ይስፈን!