صفة العمرة لابن باز
የዑምራ አደራረግ ስርዓት
የዑምራ አደራረግ ስርዓት
አዘጋጅ
ዐብዱልዐዚዝ ቢን ዐብደላህ ቢን ባዝ
ምስጋና ሁሉ ለአላህ ብቻ የተገባ ነው፤ ከዚህ በመቀጠል
ይህ የዑምራን ሥርዓት በተመለከተ አጭር ገለፃ ነው። ዝርዝር ማብራሪያው ለአንባቢያን እንደሚከተለው ቀርቧል፦
ዑምራ ማድረግ የፈለገ ሰው ሚቃት (ኢሕራም ማድረጊያ ስፍራ) ጋር ሲደርስ መታጠብና ንፅህናውን መጠበቅ ይወደድለታል። ሴት ልጅም የወር አበባ ወይም የድህረ ወሊድ ደም እያየች ቢሆንም እንኳ ተመሳሳዩን ማድረግ አለባት። ነገር ግን ከደም ንፁህ ሆና እስክትታጠብ ድረስ ጠዋፍ ማድረግ የለባትም።
አንድ ሰው የኢሕራም ልብሱን ትቶ ሰውነቱን ሽቶ ይቀባል። ሚቃት ላይ ሰውነቱን መታጠብ ካልቻለ ችግር የለውም፤ ነገር ግን ከተቻለ መካ ሲደርሱ ጠዋፍ ከማድረጉ በፊት መታጠቡ ይወደዳል።
ሰውዬው የተሰፋ ልብሱን በሙሉ አውልቆ ብትን ጨርቆችን ሽርጥ እና ኩታ ይለብሳል፤ ጨርቆቹ ንጹህ እና ነጭ ቢሆኑ ይመረጣል።
ሴቶችን በተመለከተ ግን ኢሕራም የሚያደርጉት በተለመደው ልብሳቸው ነው፤ ልብሱ ግን ጌጥና ዝና (ከሌሎች ሴቶች ወጣ ብሎ ዓይን ውስጥ መግባት) የሌለበት መሆን አለበት። (ሴቶች መሕረም ካልሆኑ /ባዳ ከሆኑ/ ወንዶች ፊታቸውንና እጆቻቸውን የሚሸፍኑት ኒቃብ፣ ቡርቃ እና ጓንት ባልሆነ ሌላ ልብስ ነው)።
ከዚያም በልቡ ወደ (ዑምራ) ስርአቱ ለመግባት አስቦ በአንደበቱ “ለበይክ ዑምረተን” ወይም “አልላሁምመ ለበይክ ዑምረተን” ብሎ ይነይታል። ኢሕራም ያደረገ ሰው ታሞ ወይም ጠላትን ወይም መሰል ነገርን በመፍራቱ የአምልኮ ሥርዓቱን ማከናወን አልችልም ብሎ ከፈራ ኢሕራም ውስጥ ሲገባ ቅድመ ሁኔታን ማስቀመጡ ተፈቅዶለታል። እንዲህም ይላል፦ "ፈኢን ሐበሰኒ ሓቢስ ፈመሐሊ ሐይሡ ሐበሰትኒይ" (ትርጉሙም)፦ "የሚያግደኝ ነገር ከተከሰተ የኢሕራሜ ፍፃሜ በታገድኩበት ቦታ ነው።" ይህም የዱባዐህ ቢንት አዝ'ዙበይር አላህ መልካም ሥራዋን ይውደድላትና ሐዲሥን በመመርኮዝ ነው። [1] አል-በይሀቂይ ሱነን አል-ኩብራ (ቁጥር 10117)
ከዚያም ነብዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ያደረጉትን ዓይነት ተልቢያ ያደርጋል እርሱም፦ "ለብበይከ አልላሁምመ ለበይክ፤ ለበይከ ላ ሸሪከ ለከ ለበይክ፤ ኢነል ሐምደ፤ ወንኒዕመተ፤ ለከ ወልሙልክ፤ ላ ሸሪከ ለከ ለበይክ" ትርጉሙም፡ (አላህ ሆይ ጥሪህን ደጋግሜ አቤት ብያለሁ! አሁንም ደጋግሜ ጥሪህን አቤት ብያለሁ አላህ ሆይ! አንተ አጋር የለህም። ምስጋና፣ ፀጋና ንግስናም ለአንተ ነው። አጋር የለህም።» ይህንን ተልቢያ፤ ኃያሉን አላህ ማውሳትን እና ዱዓ ማድረግን ወደ ቤቱ (ካዕባ) እስኪደርስ ድረስ ያበዛል። «ለበይከል-ሏሁምመ ለበይክ፤ ለበይከ ላ ሸሪከ ለከ ለበይክ፣ ኢንነል-ሐምደ ወን-ኒዕመተ ለከ ወል-ሙልክ፤ ላ ሸሪከ ለክ» (ትርጉሙ፦ "አላህ ሆይ! ጥሪህን ተቀብያለሁ፤ አሁንም! ጥሪህን ተቀብያለሁ፤ ላንተ አጋር የለህም፤ ምስጋና ሁሉ፤ ጸጋም ሁሉ፤ ንግስናም ላንተ ብቻ ነው፤ አጋር የለህም።") ወደ ከዕባ እስኪደርስ ድረስም ይህችን ተልቢያህ፤ የአላህን ስም ማውሳት (ዚክር) እና አላህን መለመን (ዱዓ) ማብዛት ይኖርበታል።
(ማስታወሻ፦ ወንዶች ድምጻቸውን ከፍ ያደርጋሉ፤ ሴቶች ደግሞ ድምጻቸውን ዝቅ ያደርጋሉ። ይህም ሰሐባዎች ያደርጉት እንደነበረው ነው።)
የአላህ ቤት (ካዕባ) ጋር ሲደርስ ተልቢያ ማለቱን አቁሞ ወደ ሐጀረል አስወድ (ጥቁሩ ድንጋይ) ይሄድና የሚመችና ሰዎችን በማጨናነቅ (በመገፋፋት) የማያስቸግር ከሆነ አጠገቡ በመሆን በቀኝ እጁ ይዳብሰዋል ይስመዋልም። ሰላምታን በሚያቀርብ ጊዜም እንዲህ ይላል፡ "ቢስሚላሂ አላሁ አክበር" (በአላህ ስም፤ አላህ ታላቅ ነው)፤ መሳም የማይመቸው ከሆነ በእጁ፣ በዱላ ወይም መሰል ነገር መንካትና የነካበትን ነገር መሳም ይችላል። መንካት የሚከብድ ከሆነ ወደ ሐጀረል አስወድ በመጠቆም “አላሁ አክበር" (አላህ ታላቅ ነው) ይበል ያመላከተበትን እጁን ግን አይስምም።
ጠዋፉ ትክክለኛ ይሆን ዘንድ ጠዋፍ የሚያደርገው ሰው ከትንሹም (ዉዱእ ማድረግ ከሚያስፈልገው) ሐደሥም ሆነ ከትልቁ (ገላ ትጥበት ከሚያስፈልገው) ሐደሥ ንፁህ መሆን አለበት። ምክንያቱም ጠዋፍ ሥርዓቱን በሚያከነውኑ ጊዜ መናገር ተፈቀደ እንጂ ልክ እንደ ሰላት ነውና።
ካዕባን በግራው በኩል አድርጎ ሰባት ዙር ጦዋፍ ያደርጋል (ካዕባን ይዞራል)። ሩክነል የማኒ ጋር ሲደርስ ከቻለ በቀኝ እጁ ይነካውና እንዲህ ይላል፦ “ቢስሚላህ ወላሁ አክበር” ነገር ግን አይስመውም። እሱን መንካት የሚያስቸግረው ከሆነ ግን ወደ እሱ ሳይጠቁም ወይም “አላሁ አክበር” ሳይል ትቶ ዙሩን መቀጠል ይኖርበታል። ምክንያቱም ይህ ከነቢዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) አልተላለፈምና ነው።
ሐጀረል አስወድን (ጥቁሩን ድንጋይ) ግን እርሱ ጋር በደረሰ ቁጥር ቀደም ሲል እንደጠቀስነው እየነካው ይስመዋል ካለበለዚያ እየጠቆመ አላሁ አክበር ይላል። በመጀመሪያዎቹ ሶስት የጠዋፍ አል-ቁዱም (መካ የመግባት ጠዋፍ) ዙሮች በተለይም ለወንዶች በሶምሶማ ማለትም እርምጃዎችን ከማቀራረብ ጋር ፈጠን ያለ አረማመድ መራመዱ ይወደዳል። ለወንድ ልጅ ብቻ በጠዋፈል ቁዱም የመጀመሪያዎቹ ሶስት ዙሮች ላይ ረመል ማድረግ የተወደደ (ሙስተሐብ) ነው። ረመል ማለት እርምጃን በማቀራረብ ፈጠን ብሎ መሄድ ነው።
እንዲሁም ለወንድ ልጅ በጠዋፍ አል-ቁዱም ዙሮች ሁሉ "የኢድጢባዕ" አለባበስ መልበስ ይወደድለታል። "ኢድጢባዕ" ማለት: የኩታውን መሃል ቀኝ ብብቱ ስር በመክተት የኩታውን ጫፎች በግራ ትከሻው ላይ ማድረግ ነው። ኢድጢባዕ (ትከሻን መግለጥ)፦ ወንድ ልጅ በሰባቱም የጠዋፍ ዙሮች ላይ የላይኛውን የኢሕራም ልብስ (ሪዳእ/ የኩታውን) መሃሉን በቀኝ ትከሻው ስር አሳልፎ ሁለቱን ጫፎች በግራ ትከሻው ላይ በማድረግ ቀኝ ትከሻውን ገልጦ መተው ነው።
በሁሉም ዙሮች ውስጥ በተቻለ መጠን ዚክር (አላህን ማውሳት) እና ዱዓእ (አላህን መለመን) ማብዛቱ ይወደዳል።
በጠዋፍ ወቅት የሚደረግ የተለየ ዱዓም ሆነ ዚክር የለም፤ ስለዚህም አንድ ሰው የፈለገውን ዓይነት አዝካር እና ዱዓእ ማድረግ ይችላል። በሩክነል የማኒ እና ሐጀረል አስወድ መካከል ሲደርስ ግን (ረብበና አቲና ፊ ዱንያ ሐሰነተን ወፊልአኺረቲ ሐሰነተን ወቂና ዓዛበን-ናር) ይበል (ትርጉሙም)፦ ጌታችን ሆይ! በምድረ ዓለም ደግን ነገር (ጸጋን) በመጨረሻይቱም አገር ደግን ነገር (ገነትን) ስጠን፤ የእሳትንም ቅጣት ጠብቀን [አል-በቀራህ፡ 201] ይህንንም የሚለው በእያንዳንዱ ዙር ነው፤ ምክንያቱም ነብዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) ይህን ማድረጋቸው የተረጋገጠ በመሆኑ ነው።
ሰባተኛው ዙር የሚጠናቀቀው ከተቻለ ሐጀረል አስወድን (ጥቁሩን ድንጋይ) በመንካት እና በመሳም ወይም ከላይ በተገለጸው መሰረት "አላሁ አክበር" እያለ በመጠቆም ነው። ጠዋፉን ካጠናቀቀ በኋላ ኩታውን ይለብሳል፤ (አውጥቶት የነበረውን ቀኝ እጁን በማስገባት ኩታውን) በትከሻው ላይ ያደርግና ጫፎቹን በደረቱ ላይ ያደርጋል።
ከዚያም ከተቻለ ከመቃሙ ኢብራሂም ጀርባ ሁለት ረከዓ ሰላት ይሰግዳል። ይህን ማድረግ ካልቻለ በመስጂዱ በማንኛውም ሥፍራ ይሰግዳቸዋል። ከሱረቱል አል-ፋቲሓ በኋላ፡- በመጀመሪያው ረከዓ ሱረቱል ካፊሩን በሁለተኛው ረከዓ ደግሞ ሱረቱል ኢኽላስን ያነባል። ይህ ተመራጩና በላጩ ነው፤ ነገር ግን ሌላ የቁርኣን አንቀጽ ቢያነብም ምንም ችግር የለውም። ከዚያም ሁለቱን ረከዐዎች ካጠናቀቀ በኋላ ከተቻለ ወደ ሐጀረል አስወድ ያቀናል። ሱረቱል ካፊሩን (በላቸው «እናንተ ከሓዲዎች ሆይ! 1) [አል-ካፊሩን፡ 1] በመጀመሪያው ረከዓ እንዲሁም ሱረቱል ኢኽላስ (በል «እርሱ አላህ አንድ ነው። 1) [አል-ኢኽላስ፡ 1] በሁለተኛው ረከዓ መቅራት በላጭ ነው። በሌሎች ሱራዎች ቢሰግድም ችግር የለውም። ከሶላቱ አሰላምቶ ከጨረሰ በኋላ ከተመቸው ወደ ሐጀረል አስወድ (ጥቁሩ ድንጋይ) በመሄድ በቀኝ እጁ ይነካዋል። ከሁለቱ ረከዓዎች በኋላ ከተመቸ የዘምዘም ውሃ መጠጣት ሱንና ነው።
ከዚያም ወደ አስ'ሰፋ ይሄድና (ወደ ኮረብታው) ይወጣል ወይም ስፍራው ላይ ይቆማል፤ ከተቻለ (ወደ ኮረብታው) መውጣቱ ይበልጣል፤ ከዚያም የኃያሉን አምላክን ቃል ያነባል፦ "ኢንነ-ስ-ሰፋ ወልመርወተ ሚን ሸዓኢሪልላህ" (ትርጉሙም)፦ (ሰፋና መርዋ ከአላህ /ትዕዛዝ መፈጸሚያ/ ምልክቶች ናቸው... ) (አልበቀራህ፡ 158)
(ሶፋ ላይ ከወጣ በኋላ) ወደ ካዕባ አቅጣጫ መዞሩ ይወደዳል (ከዚያም) አላህን ያመሰግናል ያልቀዋልም እንዲህም ይላል፦ (ላ ኢላሃ ኢለላህ ወሕደሁ ላ ሸሪከ ለህ፤ ለሁል ሙልኩ ወለሁል ሐምዱ ወሁወ ዐላ ኩሊ ሸይኢን ቀዲር፤ ላ ኢላሃ ኢለላሁ ወሕደህ፣ አንጀዘ ወዕደህ፣ ወነሶረ ዐብደህ፣ ወሀዘመል አሕዛበ ወሕደህ) (ትርጉሙም፡ ከአላህ በቀር በእውነት የሚመለክ አምላክ የለም፤ ለርሱም ተጋሪ የለውም፤ ንግሥናም የርሱ ብቻ ነው፤ ምስጋናም ለርሱ ብቻ የተገባው ነው፤ እርሱ በሁሉም ነገር ላይ ቻይ ነው፤ ከአላህ በቀር በእውነት የሚመለክ አምላክ የለም፤ ብቸኛ አምላክ ነው፤ ቃሉንም ፈፀመ፤ ባርያውንም ድልን አቀዳጀ፤ ብቻውን ሆኖ ስብስቦችን አሸነፈ።) ከዚያም እጆቹን ወደ ላይ በማንሳት የቻለውን ያህል ዱዓእ ያደርጋል (አላህን ይማጸናል) ይህንን ዚክር እና ዱዓእ ደግሞ ሶስት ጊዜ ደጋግሞ ይላል። "አሏሁ አክበር፤ አሏሁ አክበር፤ ላ ኢላሃ ኢለሏህ። አሏሁ አክበር፤ አሏሁ አክበር ወሊላሂል ሐምድ። ላ ኢላሃ ኢለሏሁ ወሕደሁ ላ ሸሪከ ለህ፤ ለሁል ሙልኩ ወለሁል ሐምዱ ወሁወ ዐላ ኩሊ ሸይኢን ቀዲር። ላ ኢላሃ ኢለሏሁ ወሕደህ፤ አንጀዘ ወዕደህ፤ ወነሰረ ዐብደህ፤ ወሀዘመል-አሕዛበ ወሕደህ።" (አላህ ታላቅ ነው፤ አላህ ታላቅ ነው። ከአላህ በስተቀር በእውነት የሚመለክ አምላክ የለም። አላህ ታላቅ ነው፤ አላህ ታላቅ ነው፤ ምስጋናም ሁሉ ለአላህ ነው። ከአላህ በስተቀር በእውነት የሚመለክ አምላክ የለም፤ እርሱ አንድ ነው፤ ለእርሱ አጋር የለውም። ንግስናና ምስጋና ለእርሱ ብቻ ነው፤ እርሱም በነገሩ ሁሉ ላይ ቻይ ነው። ከአላህ በስተቀር በእውነት የሚመለክ አምላክ የለም፤ እርሱ አንድ ነው። የገባውን ቃል ፈጽሟል፤ ባሪያውንም ረድቷል፤ የተሰባሰቡትንም (የጠላት) ኃይሎች ብቻውን ድል ነስቷል።) [2] የፈለገውንም ዱዓ ያደርጋል። ከዚያም ዚክርና ዱዓውን ሶስት ጊዜ ይደጋግማል። የነብዩ (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ሱንና (ትክክለኛ አርዓያ) ይህ ነው። ከዚያም ወርዶ ወደ መርዋ መራመድ ይጀምራል። ወንድ ልጅ የመጀመሪያው አረንጓዴ ምልክት ጋር ሲደርስ እስከ ሁለተኛው አረንጓዴ ምልክት ድረስ በፈጣን እርምጃ ይጓዛል። [2] ሙስሊም ዘግበውታል (ቁጥር 1218)
ሴትን ልጅ በተመለከተ አውራ (መሰተር ያለባት) በመሆኗ በደንብ መሮጧ በሸሪዓ አልተደነገገም። ከዚያም እየተራመደ ወደ መርዋን ኮረብታ ይወጣል ወይም ስፍራውው ላይ ይቆማል፤ ከተቻለ (ኮረብታው ላይ) መውጣቱ በላጭ ነው፤ ሰፋ ላይ ያለውን እና የፈፀመውን ሁሉ መርዋ ላይም ይደግማል። ከዚያም ወርዶ ሰፋ እስኪደርስ ድረስ መራመድ ባለበት ቦታ እየተራመደ መፍጠን ባለበት ቦታ ደግሞ እየፈጠነ ይጓዛል። ይህንንም ሰባት ጊዜ ይደጋግመዋል። ከሰፋ ተነስቶ መርዋ እስኪደርስ ያለው ጉዞ አንድ ዙር፤ ከመርዋ ወደ ሰፋ ሲመለስ ደግሞ ሁለተኛ ዙር (እያለ በዚህ መልኩ ይቆጥራል)። መጓጓዣ ላይ ሆኖ ሰዕይ ቢያደርግ (ከሰፋ ወደ መርዋ ቢመላለስ) ምንም ችግር የለውም፤ በተለይም አስፈላጊ በሚሆንበት ጊዜ። በተሽከርካሪ ላይ ሆኖ ሰዕይ ማድረግ ይፈቀዳል፤ በተለይ አስገዳጅ ሁኔታ ሲኖር። በሰዕይ ጊዜ የፈለገውን ዚክርና ዱዓ ማብዛት እንዲሁም ከትልቅና ከትንሽ ሐደስ ንጹሕ መሆን የተወደደ (ሙስተሐብ) ነው።
ሰዕይ (ከሰፋ ወደ መርዋ በሚመላለስበት) ወቅት ዚክር እና ዱዓእ በቻለው መጠን ማብዛቱ ተወዳጅ ነው። እንዲሁም ምንም እንኳን ያለዉዱእ ማድረጉ የሚበቃለት ቢሆንም ከትላልቅ (የገላ ትጥበትን ግዴታ ከሚያደርጉ) እና ከትናንሽ (ዉዱእ ማድረግን ግዴታ ከሚያደርጉ) ሐደሦች ንፁህ መሆን ይኖርበታል።
ሰዕዩን እንዳጠናቀቀ ወንድ ከሆነ ጭንቅላቱን ይላጫል ወይም ያሳጥራል። በላጩ መላ የጭንቅላትን ፀጉር መላጨት ነው። መካ የደረሰው የሐጅ ወቅት በተቃረበ ጊዜ ከሆነ ግን በሐጅ ወቅት የቀረውን ፀጉሩን ይላጭ ዘንድ ፀጉሩን ማሳጠር በላጭ ይሆንለታል። ሴት ከሆነች ፀጉሯን ትሰበስብና የጣት ጫፍ ወይም ከዚያ ያነሰ መጠን ትቆርጣለች። ኢሕራም ላይ ያለ ሰው ከላይ የጠቀስናቸውን ስርዓቶች ከፈፀመ የዑምራ ስርዓቱ ሙሉ ለሙሉ ይጠናቀቃል። አልሐምዱ ሊላህ (ምስጋና ሁሉ ለአላህ የተገባ ነው)። በኢሕራም ወቅት ለእርሱ እርም ተደርገው የነበሩ ነገሮች ሁሉ የተፈቀዱ ይሆኑለታል። (ነብዩ (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ዑምራን ካጠናቀቁ በኋላ ሁለት ረከዓ (የተለየ ሶላት) አልሰገዱም። እርሳቸውን የሚወድ ሰው የእርሳቸውን ፈለግ ይከተል።) (ለእናንተ አላህንና የመጨረሻውን ቀን የሚከጅል ለሆነ ሰው፣ አላህንም በብዙ ለሚያወሳ በአላህ መልዕክተኛ መልካም መከተል አልላችሁ፡፡) [አል-አሕዛብ፡ 21]
አላህ እኛንም ሆነ መላ ሙስሊም ወንድሞቻችንን ሃይማኖቱን በአግባቡ ለመገንዘብና በእርሱ ላይ ለመፅናት ያድለን፤ መልካም ሥራችንን ከሁላችንም ይቀበል። እርሱ ቸርና ለጋስ ነውና።
የአላህ ሰላትና ሰላም በባሪያውና መልዕክተኛው በነብያችን ሙሐመድ፣ በቤተሰቦቻቸው፣ በባልደረቦቻቸው እና እስከ ቂያማ ቀን ድረስ በመልካም በተከተሏቸው ላይ ሁሉ ይስፈን።
የዑምራ ስርአቶች አጭር ማጠቃለያ በ13/2/1416 ሂ ምንጭ: ከሸይኹ ጽሕፈት ቤት (የሸይኽ ኢብኑ ባዝ የፈትዋዎች ስብስብ እና መጣጥፎች 17/425)።