صفة الوضوء والصلاة (مرئي)

صفة الوضوء والصلاة (مرئي)

PROJ-187

Language: lang_am
Prepared by:
Version: 1.0
Translations 42
Akan Amharic Assamese Bengali +38
Attachments 7
PDF
Audio
Video
+3

ውዱእ እንዴት ላድርግ?

ተ.ቁ

ድምፅ

1

የአዛን ድምፅ

2

{እናንተ ያመናችሁ ሆይ! ወደ ሰላት በቆማችሁ (ለመቆም ባሰባችሁ) ጊዜ ፊቶቻችሁን፣ እጆቻችሁንም እስከ ክርኖች እጠቡ፡፡ ራሶቻችሁንም (በውሃ) አብሱ፡፡ እግሮቻችሁንም እስከ ቁርጭምጭሚቶች (እጠቡ)።}

[ሱረቱል ማኢዳህ፡ 6]

3

ያለ ዉዱእ ሰላት፤ ያለ ኒያ ዉዱእ የለም፤ ኒያ ደግሞ ኢኽላስ ከሌለው ዋጋ የለውም። ኢኽላስ ቦታዋ ልቦና ውስጥ እንጂ ምላስ ላይ አይደለም።

4

በአላህ ስም

ውዱእ ሲጀምሩ ቢስሚላህ ማለት በሸሪዓ የተደነገገ ነው፤ ዉዱእ የምንጀምረው በቢስሚላህ ነው። ከዚያም የሚመች ከሆነ አፋችንን ለማፅዳት መፋቂያ እንጠቀማለን።

5

ከጣቶቻችን ጫፍ ጀምረን እስከ እጃችን አንጓ ድረስ መዳፋችንን ሦስት ጊዜ እናጥባለን።

6

የእጃችንን አንጓ ጨምሮ ሁለቱም መዳፋችንን በተከታታይ ሶስት ጊዜ እናጥባለን።

7

መዳፋችንን ስናጥብ የምንጀምረው ሶስት ጊዜ የቀኝ እጃችንን በማጠብ ሲሆን ከዚያም አስከትለን ሶስት ጊዜ የግራ እጃችንን እናጥባለን።

8

ልክ የቀኝ መዳፍ እጃችንን ከዚያም የግራ መዳፍ እጃችንን ድጋሚ የቀኝ መዳፍ እጃችንን ከዚያም የግራ መዳፍ እጃችንን እያደረግን ማጠብ እንደምንችለው ሁሉ ማለት ነው።

9

በጣቶቻችን መሀል ውኃ እየገባ መሆኑን ማረጋገጥም ይጠበቅብናል።

10

ከዚያም ወደ መጉመጥመጥና መሰርነቅ እናመራለን።

11

መጉመጥመጥ ማለት ውኃውን አፋችን ውስጥ አድርገን በደንብ ካንቀሳቀስን በኋላ ውሀውን መትፋት ነው።

12

መሰርነቅ ማለት ደግሞ ውሀውን ወደ አፍንጫ ውስጥ በአየሩ ከሳቡ በኋላ በግራ እጅ በመናፈጥ መልኩ መልሶ ከአፍንጫ ማስወጣት ነው።

13

ሁለቱንም ስናደርግ ፆመኞች ወይም ስጋት የሚፈጥርብን ካልሆንን በቀር ውኃውን በደንብ ወደ ውስጥ መሳብ የሚበረታታ ሱና ነው።

14

መጉመጥመጥና መሰርነቅ በሁለት መልኩ ይከናወናል።

15

አል-ወስሉ (በማቆራኘት) የምንለው ዓይነት፡ አንድ እፍኝ ውሀ ይዘን ግማሹን ለመጉመጥመጥ ግማሹን ደግሞ ለመሰርነቅ የምንጠቀምበት ሲሆን

በአፋችን ውስጥ ያለውን ውሀ በደንብ እናንቀሳቅሰዋለን ከዚያም ወደ ውጪ እናስወጣዋለን፤ ከዚያም ወደ አፍንጫችን የሳብነውን ውሀ በግራ እጃችን እናስወጣዋለን።

ይህንንም ሶስት ጊዜ በሶስት እፍኝ ውሀ እናከናውናለን።

16

አል-ፈስሉ(በመለያየት) የምንለው ዓይነት ደግሞ ለመጉመጥመጥ ራሱን የቻለ እፍኝ ለአፍንጫም ራሱን የቻለ እፍኝ ውሀ መጠቀም ሲሆን ይሀውም እፍኝ ውሀ ይዘን ሙሉ በሙሉ ወደ አፋችን አስገብተን በአፋችን ውስጥ ያለውን ውሀ በደንብ እንወዘውዘዋለን ከዚያም እንተፋዋለን፤ ከዚያም ለአፍንጫችንም ሌላ እፍኝ ውሀ ይዘን ወደ አፍንጫችን እንስበውና ያንን ወደ አፍንጫችን የሳብነውን ውሀ በግራ እጃችን እናስወጣዋለን።

17

ከመጉመጥመጥና ከመሰርነቅ በኋላ ፊትን ማጠብ ይከተላል...

18

የፊት ድንበሩም ቁመት (ርዝመት)፡ ከተለመደው ፀጉር ከሚጀምርበት ግንባር እስከ አገጭ ጠርዝ ድረስ ሲሆን የጎን ስፋቱ ደግሞ በሁለቱ ጆሮዎች መካከል ነው።

19

በፊት ላይ የሚገኝን ፀጉር ሁሉ ማለትም ፂም፣ ቀድሞ ቀመስ፣ ቅንድብ፣ ሽፋሽፍት እና ከታችኛው አገጭ ስር ያለውንም ፀጉር ሁሉ ማጠብም ግዴታ ነው።

20

ፊትን ለማጠብ ሁለቱም ዘዴዎችን መጠቀም ይቻላል፡

21

የመጀመርያው፡ ሁለት እጃችንን ውሀ እንዘግናለን፤ ከዚያም በውሀው ፊታችንን ከተለመደው የፀጉር መብቀል ከሚጀምርበት እስከታችኛው የአገጭ ጠርዝ ድረስ ወደጎንም ከቀኝ ጆሮ እስከ ግራ ጆሮ ድረስ እናጥብበታለን። ፂሙ ብዙ ከሆነ በየስሩ ውሀ ማስገባትና ፈልፍሎ ማጠቡ የሚበረታታ ሱና ነው።

ይህንኑም ሶስት ጊዜ ብናደርግ የተሟላ ይሆናል። ሁለት ጊዜ ማድረግም ይቻላል። ቢያንስ አንድ ጊዜ ማድረጉ ግን ግዴታ ነው።

22

ሁለተኛው: ውሀውን በቀኝ እጃችን ብቻ ይዘን በፊታችን ላይ ካደረግን በኋላ ፊታችንን ልክ እንደመጀመርያው በሁለት እጃችን እናሻለን። ይህንንም ሶስት ጊዜ እናደርጋለን።

23

የውዱእ አካላትን ቅደም ተከተል መጠበ ግዴታ ነው። አከታትሎ ማድረጉም እንዲሁ ግዴታ ነው። በአንደኛው ቦታ ሌላኛውን ማስቀደም የለብንም። ከአንዱ የውዱእ አካል ወደ ሌላኛው ስንሸጋገርም መዘግየት የለብንም።

24

ፊታችንን ካጠብን በኋላ ሁለት እጆቻችንን ወደማጠብ እንሸጋገራለን።

25

መታጠቡ ግዴታ የሆነው የእጃችን ክፍል ከጣታችን ጫፍ እስከ ክርን ድረስ ነው፤ ክርንንም ጨምሮ ማጠብ ነው።

26

የቀኝ እጃችንን መዳፍ ከጣታችን ጫፍ ጀምሮ እናጥበዋለን፤ የሁለት እጆቻችን ጣቶች በማቆላለፍም ፈልፍለን እናጥባቸዋለን፤ ከዚያም ውሀውን እስከክርን እናዳረሰዋለን።

27

ከዚያም ወደ ግራ እጃችን በመሸጋገርም የግራ እጃችንን መዳፍ ከጣታችን ጫፍ ጀምሮ የሁለት እጆቻችን ጣቶችንም በማቆላለፍ ፈልፍለን እናጥባቸዋለን፤ ውሀውንም እስከክርን እናዳረሰዋለን።

28

ራሳችንን ወደማበስ እንሸጋገር: እጆቻችንን እንደ አዲስ ውሀ በመዝገን እናረጥባቸዋለን፤ ከዚያም እነዚያ ያረጥብናቸው እጆቻችንን ከግንባራችን ጀምረን እሰከማጅራታችን ድረስ እንዳብስባቸዋለን። ከዚያም ወደተነሳንበት ቦታ እንመልሳቸዋለን። ራስን ለማበስ በምናዳርሰው ድንበር በኩል በራሰ በራ እና ፀጉር ባለው ሰው መካከል ልዩነት የለም።

29

ከዚያም ራሳችንን ካበስንበት በተቀረው ውሀ ሁለት ጆሮዎቻችንን እናብስበታለን። ይህንን የምናደርገው አንድ ጊዜ ብቻ ነው።

30

ጆሮዎቻችንን የማበስ አኳኋኑም ጠቋሚ ጣትን በጆሮ ቀዳዳ ውስጥ ካስገቡ በኋላ በዛው የውስጡን ክፍል በማሸት፤ በአውራ ጣት ደግሞ የጆሮ የላይኛውን ክፍል ማበስ ነው። በዚህም የጆሯችንን ላይኛውንም ውስጠኛውንም ክፍል አበስን ማለት ነው።

31

ከዚያም ሁለት እግሮችን ወደ ማጠብ እንሸጋገራለን፡ ማጠቡ ግዴታ የሚሆነው የእግራችን ክፍል ከእግሮቻችን ጣቶች ጫፍ እስከ ቁርጭምጭሚት ድረስ ነው። ቁርጭምጭሚቶችንም ማጠብ ግዴታ ነው።

32

ከቀኝ እግር ጀምረን በየጣቶቻችን መካከል እየፈለፈልን ቁርጭምጭሚታችንንም ይሁን ከተረከዛችን በላይ በኩል ያለውንም ትኩረት ሰጥተን እናጥበዋለን።

33

ከዚያም ልክ የቀኝ እግራችንን እንዳጠብነው አድርገን የግራ እግራችንንም በሚገባ እናጥበዋለን። በየጣቶቻችን መካከል እየፈለፈሉ ማጠብ አለመርሳት፤ ተረከዛችንን በተሟላ መልኩ ማጠባችንን እንዲሁም ቁርጭምጭሚታችን ድረስ ውሀ መዳረሱንም ማረጋገጥ መቻል አለብን።

34

"አሽሀዱ አን ላኢላሃ ኢለሏህ ወሕደሁ ላ ሸሪከ ለሁ ወአሽሀዱ አነ ሙሐመደን ዐብዱሁ ወረሱሉህ" ትርጉሙም: ከአላህ በስተቀር በእውነት የሚገዙት አምላክ እንደሌለና ተጋሪ የሌለው ብቸኛ መሆኑን እመስክራለሁ፤ ሙሀመድም የአላህ መልዕክተኛው እና ባሪያው መሆናቸውንም እመስከራለሁ።

35

ውዱእ ካጠናቀቁ በኋላ ዱዓእ እና ዚክር ማለት የሚበረታታ ሱና ነው። (ከፍ ብሎ የተጠቀሰውን ካለ በኋላ) ተከታዩን ቢጨምር ይበልጥ የሚበረታታ ሱና ነው።

36

"አልላሁምመጅዓልኒ ሚነ ተዋቢነ ወጅዓልኒ ሚነል ሙተጠሂሪን" ትርጉሙም: አሏህ ሆይ! በተውባ ወዳንተ ከሚመለሱትና ፅዳታቸውንም ከሚጠብቁት አድርገኝ።

37

ወይም:

"ሱብሐነከላሁምመ ወቢሐምዲከ፡ አሽሀዱ አንላ ኢላሀ ኢላ አንተ፡ አስተግፊሩከ ወ አቱቡ ኢለይከ" ትርጉሙም፦ አሏህ ሆይ! ጥራትና ምስጋና ላንተ ይገባህ፤ ከአንተም ውጭ በእውነት አምልኮ የሚገባው አምላክ እንደሌለ እመሰክራለሁ፤ መሀርታህንም እማፀንሀለሁ፤ በፀፀትም ወደ አንተው እመለሰላሁ።

ተ.ቁ

ስክሪን ላይ የተፀፈ

1

ውዱእ እንዴት ላድርግ?

2

{እናንተ ያመናችሁ ሆይ! ወደ ሶላት በቆማችሁ (ለመቆም ባሰባችሁ) ጊዜ ፊቶቻችሁን፣ እጆቻችሁንም እስከ ክርኖች እጠቡ፡፡ ራሶቻችሁንም (በውሃ) አብሱ፡፡ እግሮቻችሁንም እስከ ቁርጭምጭሚቶች (እጠቡ)።}

[ሱረቱል ማኢዳህ፡ አንቀፅ ቁጥር 6]

3

ሁለቱን መዳፎች ማጠብ

4

መጉመጥመጥና መሰርነቅ

5

በማቆራኘት

6

በመለየት

7

ፊትን ማጠብ

8

የመጀመርያው

9

ሁለተኛው

10

ኒያ እና ቢስሚላህ ማለት

11

ሁለቱን መዳፎች ማጠብ

12

መጉመጥመጥ

13

መሰርነቅ

14

ፊትን ማጠብ

15

ሁለት እጆችን ከክርን ጋር አብሮ ማጠብ

16

ጭንቅላትን ማበስና ሁለት ጆሮዎችንም ማበስ

17

ሁለት እግሮችን ቁርጭምጭሚትን ጨምሮ ማጠብ

18

ሁለት እጆችን ማጠብ

19

የራስ ቅልን ማበስ

20

የራስ ቅል የሚታበስበት መነሻ ቦታ = በግንባር በኩል በተለምዶ ፀጉር ከሚበቅልበት ቦታ ይጀምራል...

21

የራስ ቅል የሚታበስበት መጨረሻ ቦታ = ከማጅራት በኩል ፀጉር ከሚያልቅበት ቦታ ላይ ያበቃል...

22

ሁለት ጆሮዎችን ማበስ

23

ሁለት እግሮችን ማጠብ

24

ነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን እንዲህ ብለዋል፦

«ለተረከዞች ከእሳት (ቅጣት) ወየውላቸው፤ ውዱእ ስታደርጉ አዳርሱ»

አቡዳውድ ዘግበውታል።

25

"አሽሀዱ አን ላኢላሃ ኢለላህ ወሕደሁ ላ ሸሪከ ለሁ ወአሽሀዱ አነ ሙሐመደን ዐብዱሁ ወረሱሉህ" ትርጉሙም: ከአላህ በስተቀር በእውነት የሚገዙት አምላክ እንደሌለና ተጋሪ የሌለው ብቸኛ መሆኑን እመስክራለሁ፤ ሙሐመድም የአላህ መልዕክተኛው እና ባሪያው መሆናቸውንም እመስከራለሁ።

ሙስሊም ዘግበውታል።

26

"አልላሁምመ ኢጅዓልኒ ሚነ አትተዋቢነ ወጅዐልኒ ሚነል ሙተጠሂሪን።" ትርጉሙም፦ "አላህ ሆይ! ከኃጢአት በንሰሀ ተመላሽ ከሆኑት ሰዎች ጎራ አድርገኝ፤ ከተጥራሪዎች (ራሳቸውን በብዛት ከሚያጸዱ) ሰዎች ጭፍራም አድርገኝ።"

ቲርሚዚይ ዘግበውታል።

27

"ሱብሐነከላሁምመ ወቢሐምዲከ አሽሀዱ አን ላ ኢላሃ ኢላ አንተ አስተግፊሩከ ወአቱቡ ኢለይክ" (ትርጉሙም: ‹‹አላህ ሆይ! ጥራት ላንተ ተገባ፤ ምስጋናም ላንተ ይሁን፤ ካንተ በስተቀር ሌላ በእውነት የሚመለክ አምላክ አለመኖሩን እመሰክራለሁ፤ ምሕረትህንም እለምነሃለሁ፤ ከኃጢኣቴ ተጸጽቼ ወደ አንተ እመለሳለሁ፡፡››

ነሳኢይ በ "ዐመሊል የውሚ ወለይላ" በተሰኘው ኪታባቸው ዘግበውታል።

እንዴት ልስገድ?

ሰላት በተክቢር (አላሁ አክበር) በሚለው ቃል ተጀምሮ በተስሊም (አስ’ሰላሙ ዐለይኩም) በሚለው ቃል የሚያበቃ (ዒባዳ (አምልኮ) ነው።

ተ.ቁ

ድምፅ

1

የሰላት ኢቃም ድምፅ

2

የኢቃም ድምፅ በዘላቂነት

ኒያን (ልባዊ ወሳኔን) ማስገኘት፤ ይህም የሚሰግድ ሰው በቅድሚያ የሚያከናውነው ነገር ሲሆን ቦታውም ልብ ውስጥ ነው።

3

ወደ ቂብላ እንቅጣጫለን፤ ኢማም ሆነህ ወይም ለብቻህ እየሰገድክ ከሆነ በፊት ለፊትህ ሱትራ (መከለያ) አድርግ።

4

"አላሁ አክበር" ትርጉሙም፡ አላህ ታላቅ ነው

ተክቢረቱል ኢሕራም፤ ሰላት የሚጀመረው በእርሷ ነውና በአንደበት ቃሉን ማለቱ ግዴታ ነው።

5

"አላሁ አክበር" በምንልበት ጊዜ እጆቻችንን በትካሻችን ትይዩ ከፍ እናደርጋለን፤ መዳፋችንን ደግሞ ወደ ቂብላ እናቅጣጨዋለን...

ወይም:

በተመሳሳይ አኳኋን ሆኖ ግን እስከ ጆሯችን ድረስ ነው ከፍ የምናደርገው።

6

"አላሁ አክበር" ካልን በኋላ ሁለቱ እጆቻችንን በደረታችን ላይ ወይም ከእምብርታችን ከፍ ብሎ ከደረታችን ስር ወይም ደግሞ ከእምብርታችን ስር ማድረግ እንችላለን። ይህ ሁሉ ትክክል ነው።

ቀኝ እጃችንን በግራ እጃችን መዳፍ ጀርባ ላይ እናስቀምጠዋለን

ወይም በቀኝ እጃችን የግራ እጃችን መዳፍ ጀርባ እንይዘዋለን

ወይም ደግሞ በቀኝ እጃችን የግራ እጃችንን አንጓ እንይዛለን

7

"አልላሁመ ባዒድ በይኒ ወበይነ ኸጣያየ ከማ ባዐድተ በይነል-መሽሪቂ ወል-መግሪቢ አልላሁመ ነቂኒ ሚን ኸጣያየ ከማ ዩነቀ-ሥ-ሠውቡል አብየዱ ሚነ ደነስ አልላሁመ 'ኢግሲልኒ ሚን ኸጣያየ ቢሥ-ሠልጂ ወልማኢ ወል-በረድ" ትርጉሙ፦ "አላህ ሆይ! በምሥራቅና በምዕራብ መካከል እንዳራራቅከው እኔንም ከወንጀሌ አርቀኝ፤ አላህ ሆይ! ነጭ ልብስ ከቆሻሻዎች እንደሚጸዳው እኔንም ከወንጀሌ አጥራኝ፤ አላህ ሆይ! እኔን ከወንጀሌ በውሃ እና በፈሳሹም በደረቁም በረዶ እጠበኝ።"

ልክ ተክቢረተል ኢሕራም እንዳደረግን ቁርኣን ከመቅራታችን በፊት የመክፈቻ ዱዓእ እናደርጋለን፤ ከዚህም ውጭ የመክፈቻ ዱዓእ ከነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን በተለያየ መልኩ የመጣ ስላለ እየቀያየሩ ማለቱ የሚበረታታ ሱና ነው።

8

"አዑዙ ቢላሂ ሚነ ሸይጣኒ-ር-ረጂም" ትርጉሙም፦ "ከተረገመው ሰይጣን በአላህ ስም እጠበቃለሁ።"

ከመክፈቻ ዱዓእ በኋላ (አዑዙ ቢላህ የሚለውን) ከሸይጧን መጠበቂያ በማለት ከዚያም ሱረቱል ፋቲሓን መቅራት ነው።

9

እያንዳንዷን አንቀፅ እየለያየን በተመስጦ እና በእርጋታ መቅራት ይገባል።

10

ኣሚን

ኢማም ሆኖ ለሚያሰግድም፣ ተከታይ ሆኖ ለሚሰግድም ይሁን ብቻውን ለሚሰግድ ሰው (ኣሚን) ማለቱ የሚበረታታ ሱና ነው። ይህ ቃል የሱረቱል ፋቲሓ አንቀፅ አካል አይደለም፤ ይልቁንም "አላህ ሆይ! ዱዓችንን ተቀበለን" የሚል መልዕክት ያለው ዱዓእ ነው።

11

ከፋቲሓ በኋላም ከቁርኣን የገራልንን የተወሰኑ አናቅፅ ወይም ሙሉ ሱራ እንቀራለን፤ ምእራፉን ቀርተን እንዳጠናቀቅን ወደ ሩኩዕ ከመሸጋገራችን በፊት ለጥቂት ጊዜ በጥሞና እንቆያለን።

12

"አላሁ አክበር" ትርጉሙም፡ አላህ ታላቅ ነው!

ከዚያም ከቆምንበት ወደ ሩኩዕ ለመውረድ መሸጋገሪያ "አላሁ አክበር" እያልን እንወርዳለን።

ነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን በሰላት ውስጥ ሆነው ሁለት እጃቸውን ከፍ የሚያደርጉበት ሁለተኛው ቦታ ይህ ነበር። በመሆኑም ሁለት እጃቸንን በትከሻችን ወይም በጆሯችን ትይዩ ከፍ ልናደርግ ይገባል።

13

ሁለት እጆቻችንን ልክ የሚይዝ እንደሚመስል ጣቶቻችንን ከፈትፈት አድርገን በጉልበታችን ላይ እናስቀምጣቸዋለን።

በሩኩዓችንም እርጋታን በመላበስ እጆቻችንንም ከጎናችን እናርቃለን፤ ወደ አንዱ ጎናችን በማዘንበል ጉንጯን አንወጣም።

14

ጀርባችንም ሳይጎብጥ ለጥ ያለ እናደርገዋለን፤ ጭንቅላታችንም ከፍም ሳይል ዝቅም ሳይል ከወገባችን ጋር እኩል ትይዩ እናደርገዋለን።

15

«ሱብሐነ ረቢየል ዐዚም» ትርጉሙም፡ ለኃያሉ ጌታዬ ጥራት (ልቅና) ይገባው።

(ከላይ ባለው አገላለፅ) አላህ ማጥራታችንንም ሶስት ጊዜ እንደጋግመዋለን፤ አንድ ጊዜ ብቻም ማጥራቱ በቂ ነው፤ የምንጨምረው በፍላጎታችን ነው። ከነቢዩ የመጡትን የተስቢሕ አደራረጎች እያቀያየሩ ማለቱ ይበልጥ ተመራጭ ነው።

16

በሩኩዕ ጊዜ የሚባሉት የዚክር አይነቶች በርካታ ናቸው።

17

"ሰሚዐላሁ ሊመን ሐሚዳህ" ትርጉሙም፡ አላህ የሚያመሰግኑትን ሰማ!

ይህንን የምንለው ከሩኩዕ ቀና በምንልበት ጊዜ ሲሆን ይኸውም ብቻችንን በምንሰግድበት ወይም ኢማም ሆነን በምናሰግድበት ሁኔታ ላይ ስንሆን ነው።

18

በትከሻችን ትይዩ ወይም በጆሮዎቻችን ትይዩ ሁለት እጆቻችንን ከፍ እናደርጋለን። ይህም ሁለት እጆቻችንን ከፍ የምናደርግበት ሶስተኛው ቦታ መሆኑ ነው።

19

ከዚያም እንዲህ እያልን ከሩኩዑ ቀና እንላለን፡

"ረበና ወለከል ሐምድ" ትርጉሙም፡ ጌታችን ሆይ! ምስጋና ላንተ ይሁን

20

ሩኩዕ ካደረግን በኋላም ሁለት እጆቻችንን ማጣመርም ሆነ መልቀቅም እንችላለን።

21

ከሩኩዕ በኋላ ዘለግ ላለ ጊዜ መቆሙም በዛውም ሰከን ማለቱ የሚበረታታ ሱና ነው።

22

"አላሁ አክበር" ትርጉሙም፡ አላህ ታላቅ ነው።

ከዚያም ከቆምንበት ወደ ሱጁድ የምንወርድበትን የመሸጋገሪያ "አላሁ አክበር" ብለን ወደ መሬት እንወርዳለን።

ሁለት እጆቻችንን ከጉልበታችን በፊት መሬት ላይ እናስቀምጣቸዋለን፤ ወይም ደግሞ ጉልበታችንን ከሁለት እጆቻችን በፊት እናስቀምጣቸዋለን፤ ከሁለቱ ይበልጥ የገራልንን ማስቀደም እንችላለን።

23

ልክ የአላህ መልዕክተኛ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን እንዳስተማሩን በሰባት የሰውነት አካላችን ሱጁድ ልናደርግ ይገባል፤

በግንባራችን አፍንጫችንን ጨምሮ፣ በሁለቱ መዳፎቻችን፣ በሁለቱ እግሮቻችን (የእግር ጣት ጫፎች) እና በሁለቱ ጉልበታችን መሆን አለበት።

24

የእግሮቻችን ጣት ጫፎች ወደቂብላ አቅጣጫ አድርገን እግራችንን እንተክላለን።

ጭኖቻችንን እንለያያለን፤ ሆዳችንንም ከነርሱ ከፍ እናደርገዋለን።

ጀማዓ የምንሰግድ ሆነን በዙሪያችን ያሉትን የምናስቸግር እስካልሆንን ድረስ ክንዳችንን ከመሬት ወደ ላይ ከፍ አድርገን ከጎናችን እናርቃቸዋለን።

መዳፎቻችንንም በትከሻችን ወይም በጆሯችን ትይዩ እናደርጋለን።

25

«ሱብሓነ ረቢየል አዕላ» ትርጉሙም፡ ‹‹ከሁሉ በላይ የላቀው ጌታዬ ጥራት ይገባው››

(ከላይ ባለው አገላለፅ) አላህን ማጥራታችንን ሶስት ጊዜ እንደጋግመዋለን፤ ቢያንስ የሚባለው ሙሉ ሶስቴ ነው። አንድ ጊዜ ብቻም ማለትም በቂ ነው፤ የምንጨምረው በፍላጎታችን ነው። ከነቢዩ የመጡትን የተስቢሕ አደራረጎች እያቀያየርን እንላለን። ከዱኒያም ከኣኺራም የምንፈልገውን መልካም ነገር እንለምነዋለን።

26

የአላህ መልእክተኛ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን እንዲህ ብለዋል፦ «አንድ የአላህ ባርያ ወደ ጌታው ይበልጥ ቅርብ የሚሆነው ሱጁድ ላይ ሲሆን ነውና ሱጁድ ላይ ስትሆኑ ዱዓእ አብዙ።»

27

"አላሁ አክበር" ትርጉሙም፡ አላህ ታላቅ ነው!

"አላሁ አክበር" እያልን ከሱጁድ ቀና እንላለን።

ግራ እግራችንን አንጥፈነው ተረጋግተን እንቀመጥበታለን፤ ቀኝ እግራችንን ደግሞ ጣቶቹን ወደ ቂብላ አቅጣጭተን እንተክለዋለን።

ወይም:

ሁለቱንም እግሮቻችንን ተክለን ተረከዛችን ላይ እንቀመጣለን።

ቀኝ ክንዳችንን በቀኝ ታፋችን ላይ እንዘረጋለን፤ የግራ ክንዳችንንም እንዲሁ በግራ ታፋችን ላይ እንዘረጋለን፤ ጉልበታችን ጋ ወይም ጉልበታችን ላይ እንዘረጋዋለን።

28

"ረቢግፊርሊ" ትርጉሙም: ጌታዬ ሆይ ምህረትህን!

በሁለት ሱጁዶች መሀል ተረጋግተን ስንቀመጥ የምንፀልይበት (የምንለምንበት) ነው።

29

"አላሁ አክበር" ትርጉሙም፡ አላህ ታላቅ ነው!

"አላሁ አክበር" እያልን ለሁለተኛው ሱጁድ እንወርዳለን፤ ይህም በአኳኋንም በንግግርም ልክ እንደመጀመርያው ሱጁድ ነው። (በተመሳሳይ መልኩ ነው የምንፈጽመው)

30

"አላሁ አክበር" ትርጉሙም፡ አላህ ታላቅ ነው!

ልክ በመጀመሪያው ሩኩዕ ላይ እንዳደረግነው በሁለተኛው ሩኩዕም እንደዛው እናደርጋለን።

ሁለት እጆችን በደረት ማስቀመጥ፤ ፋቲሓን መቅራት እና የተወሰኑ የቁርኣን አናቅፅ መቅራት ነው።

ከዚያም ሩኩዕ

"አላሁ አክበር" ትርጉሙም፡ አላህ ታላቅ ነው

ከዚያም እንቆማለን

"ሰሚዐላሁ ሊመን ሐሚዳህ" ትርጉሙም፡ ‹‹አላህ የአመስጋኝን ምስጋና ሰሚ ነው፡፡››

ከዚያም ወደ ሱጁድ እንወርዳለን

"አላሁ አክበር" ትርጉሙም፡ አላህ ታላቅ ነው!

ሁለት ሱጁድ አድርገን ከዚያም ለተሸሁድ እንቀመጣለን

"አላሁ አክበር" ትርጉሙም፡ አላህ ታላቅ ነው!

"አላሁ አክበር" ትርጉሙም፡ አላህ ታላቅ ነው!

"አላሁ አክበር" ትርጉሙም፡ አላህ ታላቅ ነው!

31

ሁለተኛውን ረከዓ እንዳጠናቀቅንም ለተሸሁድ መቀመጥ ይጠበቅብናል፤ ስንቀመጥ "ኢፍቲራሽ" በሚባለው አቀማመጥ እንቀመጣለን።

32

"ኢፍቲራሽ" የሚባለው አቀማመጥ ሱብሒ፣ ጁሙዓ፣ ዒድ መሰል ሁለት ረከዓህ በሚሰገድባቸው ሰላቶች ላይ እና ሶስትና አራት ረከዓህ በሚሰገድባቸው ሰላቶች የመጀመሪያው ተሸሁድ ላይ እንዲሁም በሁለቱ ሱጁዶች መከካል ስንቀመጥ የምንቀመጥበት አቀማመጥ ነው።

33

በሰውነቱ ግዙፍነት ወይም እግሩ ላይ ባለበት ህመም ወይም ደግሞ በሌላም ምክንያት "ኢፍቲራሽ" የሚባለውን አቀማመጥ መቀመጥ ካልቻለ በየትኛውም የሚችለው አቀማመጥ ቢቀመጥ ችግር የለውም።

34

ለተሸሁድ በምንቀመጥበት ጊዜ የቀኝ እጃችንን ከጠቋሚ ጣት ውጭ ያሉትን ጣቶች ሰብስበናቸው በጠቋሚ ጣታችን በማመላከት በቀኝ ታፋችን ላይ እናስቀምጠዋለን።

35

ወይም ደግሞ አውራ ጣታችንን ከመሀል ጣታችን ጋር ክብ ሰርተንበት በጠቋሚ ጣታችን እናመላክታለን።

36

የግራ እጃችን በግራ ታፋችን ላይ እንዘረጋዋለን፤ አልያም ጉልበታችንን እንይዝበታለን።

ተሸሁድ በምናደርግበት ጊዜ ዓይናችን ማረፍ ያለበት በቀኝ እጃችን ጠቋሚ ጣት ላይ መሆኑ የሚወደድ ነው።

37

“አት‐ተሒያቱ ሊላሂ ወስ‐ሶላዋቱ ወጥ‐ጠይ‐ዪባቱ፣ አስ‐ሰላሙ ዐለይከ አይዩሀን-ነቢይዩ ወረሕመቱልላሂ ወበረካትሁ፤ አስሰላሙ ዐለይና ወዓላ ዒባዲላሂ አሷሊሒን አሽሀዱ አንላኢላሀ ኢለላህ ወአሽሀዱ አንነ ሙሐመደን ዐብዱሁ ወረሱሉሁ።” “ትርጉሙም: ክብርና ልዕልና እንዲሁም ሰላቶችና መልካም ነገሮች ሁሉ ለአላህ ናቸው። አንቱ ነቢዩ ሆይ! የአላህ ሰላም፣ እዝነቱና በረከቶች በእርሶ ላይ ይስፈን፤ ሰላም በእኛና በአላህ ደጋግ ባሮችም ላይ ይስፈን፤ ከአላህ ሌላ በእውነት የሚመለክ አምላክ እንደሌለ እመሰክራለሁ፤ ሙሐመድም የአላህ ባርያና መልዕክተኛው መሆናቸውንም እመሰክራለሁ።”

ሰላቱ ሶስት ረከዓህ ወይም አራት ረከዓህ የሚሰገድበት ከሆነ የመጀመርያውን ተሸሁድ ብቻ ብንል በቂ ነው።

ሰላቱ እንደ ሱብሒ፣ ጁሙዓህ፣ ሁለቱ ዒዶች መሰለ ሁለት ረከዓህ የሚሰገድበት ከሆነ ግን (ተከታዩን) ሰላቱል ኢብራሂሚያን በማለት ማሟላት አለብን።

"አላሁምመ ሰሊ ዐላ ሙሐመዲን ወዓላ ኣሊ ሙሐመዲን ከማ ሰለይተ ዐላ ኢብራሂም ወዐላ ኣሊ ኢብራሂም፤ ወባሪክ ዓለ ሙሐመዲን ወዐላ ኣሊ ሙሐመዲን ከማ ባረክተ ዐላ ኢብራሂም ወዐላ ኣሊ ኢብራሂመ ኢነከ ሐሚዱን-መጂድ።" (ትርጉሙም፡ አላህ ሆይ! ሰለዋትህን (ውዳሴህን) በሙሐመድና በሙሐመድ ቤተሰብ ላይም አድርግ፤ ልክ በኢብራሂም እና በኢብራሂም ቤተሰቦች ሰለዋት (ውዳሴህን) እንዳደርግከው ሁሉ፤ አንተ ምስጉን የተከበርክ ነህና። አላህ ሆይ! በረከትህንም በሙሐመድ እና በሙሐመድ ቤተሰቦች ላይም አድርግ ልክ በኢብራሂምና በኢብራሂም ቤተሰቦች እንዳደረግከው፤ አንተ ምስጉን የተከበርክ ነህና።)

38

"አስሰላሙ ዐለይኩም ወረሕመቱላህ" ትርጉሙም: የአላህ ሰላም እና እዝነት በእናንተ ላይ ይሁን!

"አስሰላሙ ዐለይኩም ወረሕመቱላህ" ትርጉሙም: የአላህ ሰላም እና እዝነት በእናንተ ላይ ይሁን!

ይህ (ከፍ ብሎ የተጠቀሰው) ማሰላመት ተሸሁድንና ከነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን የመጡትን ዱዓዎች ማድረጋችንን ካጠናቀቅን በኋላ የምንለው ነው። ይህ ግን ሁለት ረከዓህ ብቻ በሚሰገድባቸው ሰላቶች ከሆነ ነው።

39

በስሱ ውዳሴዎችን እናሰማለን፡ አላሁ አክበር

ነገር ግን ሰላቱ እንደ መግሪብ ሶስት ወይም እንደ ዙህር፣ ዓሱር እና ዒሻእ አራት ረከዓህ ከሆነ

40

መግሪብ ከሆነ የምንሰግደው አንድ ረከዓህ ለመጨመር፤ ዙህር ወይ ዓሱር ወይም ዒሻእ ከሆነ ደግሞ ሁለት ረከዓህ ለመጨመር እንቆማለን። በዛውም ፋቲሓንም እንቀራለን፤ በሩኩዕም በሱጁድም በመቆምም ባሳለፍነው መልኩ በተመሳሳይ ሁኔታ እናደርጋለን።

41

"አላሁ አክበር" ትርጉሙም፡ አላህ ታላቅ ነው!

42

ነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን ሁለት ተሸሁድ ባላቸው ሰላቶች ሁሉ በሁለተኛው ተሸሁድ የሚቀመጡት "ተወሩክ" በተሰኘው አቀማመጥ ነው።

43

"ተወሩክ" የተሰኘው አቀማመጥ ሶስትና አራት ረከዓህ ባላቸው ሰላቶች በመጨረሻው ተሸሁድ ላይ ብቻ የሚቀመጡበት አቀማመጥ ነው። አኳኋኑም የተለያየ ዓይነት አለው።

44

የቀኝ እግር ተረከዝን መትከል (ማቆም)፤ የግራ እግርን ተረከዝ ደግሞ መሬት ላይ አንጥፎ በተተከለው የቀኝ እግር አሽሉኮ በቀኝ በኩል እንዲወጣ በማድረግ መሬቱ ላይ መቀመጥ ነው።

ወይም:

የሁለቱንም እግሮች ተረከዝ መሬት ላይ ዘርግቶ በቀኝ በኩል እንዲወጡ ማድረግ ነው።

ወይም:

የቀኝ እግርን ተረከዝ መሬቱ ላይ አንጥፎ የግራ እግርን ተረከዝ ደግሞ በቀኝ እግር ተረከዝና በታፋ መካከል አድርጎ መቀመጥ ነው።

45

ለመጨረሻው ተሸሁድ በመተቀመጥንበት ጊዜ ተሸሁድ ካደረጉ በኋላ በነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን ላይ ሰለዋት ማድረግ ነው።

46

ተሸሁድ ብለው ካጠናቀቅንና ከማሰላመታችን በፊት ከአራት ነገሮች በአላህ እንጠበቃለን፦ ከእሳት ቅጣት፣ ከቀብር ቅጣት፣ ከህይወትና ከሞት ፈተና እና ከመሲሑ ደጃል ፈተና ክፋት በአላህ እንጠበቃለን።

ከዚያም ከዱኒያም ከአኺራም መልካም ነገሮች እንዲሰጠን አላህን እንማፀናለን።

47

"አስሰላሙ ዐለይኩም ወረሕመቱላህ" ትርጉሙም: የአላህ ሰላምና እዝነት በእናንተ ላይ ይሁን ማለት ነው።

"አስሰላሙ ዐለይኩም ወረሕመቱላህ" ትርጉሙም: የአላህ ሰላምና እዝነት በእናንተ ላይ ይሁን ማለት ነው።

ሰላት የሚጠናቀቀውና በተክቢረተል ኢሕራም የተከለከልነው የሚቋጨው በማሰላመት ነው።

48

ካሰላመትን ሰላታችንን አጠናቀቅን ማለት ነው።

"አስተግፊሩላህ" "አስተግፊሩላህ" "አስተግፊሩላህ" (ጌታዬ ሆይ ምህረትህን)

49

የሚሰግድ ሰው ሲያሰላምት ሶስት ጊዜ (ከላይ በተጠቀሰው መልኩ) መሀርታን መለመኑ የሚበረታታ ሱና ነው። ከዚያም ጥራት የተገባውና የላቀው አላህን ከመልዕክተኛው የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን በመጡ ውዳሴዎች ሊያወድሰው ይገባል።

ተ.ቁ

ስክሪን ላይ የተፃፈ

1

ኢማም ሁነህ ብታሰግድም ሆነ ብቻህን ብትሰግድ

2

ተክቢረቱል ኢሕራም (የመክፈቻ ተክቢራ)

3

ሁለት እጆቻችንን በትከሻችን ትይዩ ከፍ እናደርጋለን

4

ወይም በተመሳሳይ አኳኋን እስከ ጆሯችን ድረስ ከፍ እናደርጋለን።

5

ሁለት እጆቻችንን በደረታችን ላይ እናደርጋለን

6

ወይም ከእምብርት ከፍ አድርገን እናስቀምጣቸዋለን።

7

ወይም ደግሞ ከእምብርት ዝቅ አድርገን እናስቀምጣቸዋለን።

8

ቀኝ እጃችንን በግራ እጃችን መዳፍ ጀርባ ላይ እናስቀምጠዋለን

9

ወይም ደግሞ በቀኝ እጃችን የግራ እጃችንን አንጓ እንይዛለን

10

የመክፈቻ ዱዓእ

11

"አላሁምመ ባዒድ በይኒ ወበይነ ኸጧያየ ከማ ባዐድተ በይነል-መሽሪቂ ወል-መግሪቢ አልላሁምመ ነቂኒ ሚን ኸጧያየ ከማ ዩነቀ-ሥ-ሠውቡል አብየዱ ሚነ ደነስ አላሁመ 'ግሲልኒ ሚን ኸጧያየ ቢሥ-ሠልጂ ወልማኢ ወል-በረድ" ትርጉሙ፦ "አላህ ሆይ! በምሥራቅና በምዕራብ መካከል እንዳራራቅከው እኔንም ከወንጀሌ አርቀኝ፤ አላህ ሆይ! ነጭ ልብስ ከቆሻሻዎች እንደሚጸዳው እኔንም ከወንጀሌ አጥራኝ፤ አላህ ሆይ! እኔን ከወንጀሌ በውሃ እና በፈሳሹም በደረቁም በረዶ እጠበኝ።"

12

የተለያዩ የመክፈቻ ዱዓዎችን እየቀያየሩ ማድረጉ የሚበረታታ ሱና ነው።

13

(አዑዙቢላህ በማለት) የአላህን ጥበቃ መሻት።

14

"አዑዙ ቢላሂ ሚነ ሸይጧኒ-ር-ሯጂም" ትርጉሙም፦ "ከተረገመው ሰይጣን በአላህ እጠበቃለሁ።"

15

ፋቲሓን ማንበብ

16

ትርጉሙ: (ምስጋና ለዓለማት ጌታ ለአላህ የተገባው ነው የዓለማት ጌታ ለሆነው። እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ፤ የፍርዱ ቀን ባለቤት ለሆነው፤ አንተን ብቻ እንገዛለን አንተንም ብቻ እርዳታን እንለምናለን። ቀጥተኛውን መንገድ ምራን፤ የእነዚያን በነርሱ ላይ በጎ የዋልክላቸውን በነሱ ላይ ያልተቆጣህባቸውንና ያልተሳሳቱትንም ሰዎች መንገድ (ምራን፤ በሉ)፡፡

17

አሚን

18

አላህ ሆይ! ልመናችንን ተቀበለን የሚል መልዕክት ያለው ዱዓእ ነው።

19

ከቁርአን የገራልንን ያህል እንቀራለን

20

ሩኩዕ

21

"አላሁ አክበር" ትርጉሙም: አላህ ታላቅ ነው!

22

ጀርባችንን ሳናወላግድ ቀጥ ማድረግ

23

«ሱብሓነ ረቢየል ዐዚም» ትርጉሙም፦ ‹‹ለኃያሉ ጌታዬ ጥራት ይገባው›

24

ከነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን ከመጡ በሩኩዕ ከሚባሉ አዝካሮች መካከል፦

25

"ሱቡሑ ቁዱስ ረቡል መላኢከቲ ወሩሕ" ትርጉሙም: ከየተኛውም እንከን የጠራ ፍፁም የመላእክትም የጅብሪልም ጌታ

26

"ሱብሓነከ ረበና ወቢሓምዲከ አሏሁመ-ግፊርሊ" ትርጉሙም: ጥራት ይገባህ ጌታችን ሆይ! የተመሰገንክ ነህ፤ አላህ ሆይ! መሀርታህን ለግሰኝ።

27

"ሰሚዐላሁ ሊመን ሐሚዳህ" ትርጉሙም፡ ‹‹አላህ የአመስጋኝን ምስጋና ሰሚ ነው፡፡››

28

"ረብበና ወለከል ሐምድ ሐምደን ከሢረን ጠይበን ሙባረከን ፊህ" ትርጉሙም: ጌታችን ሆይ! ምስጋና ላንተው ነው። እጅግ ብዙ፣ መልካም የሆነና የላቀ ምስጋና ላንተው ነው።

29

እጆቻችንን እንለቃለን

30

ወይም እናጣምራቸዋለን

31

ሱጁድ

32

ግንባር ከአፍንጫ ጋር

33

ሁለቱ መዳፎች

34

ሁለቱ ጉልበቶች

35

ሁለቱ እግሮች (የእግር ጣት ጫፎች)

36

«ሱብሓነ ረቢየል አዕላ» ትርጉሙም፡ ‹‹ከሁሉ በላይ የላቀው ጌታዬ ጥራት ይገባው››

37

«የትኛውም ባርያ ወደ ጌታው ይበልጥ ቅርብ የሚሆነው ሱጁድ ላይ ሲሆን ነውና ሱጁድ ላይ ስትሆኑ ዱዓእ አብዙ።» ሙስሊም ዘግበውታል.

38

"ኢፍቲራሽ" የተሰኘው አቀማመጥ

39

"ኢቅዓእ" የተሰኘው አቀማመጥ

40

"ረብቢግፊርሊ" (ሶስት ጊዜ)፤ ትርጉሙም: ጌታዬ ሆይ ምህረትህን ማለት ነው።

41

"አልላሁምመ-ግፊርሊ ወርሐምኒ ወጅቡርኒ ወህዲኒ ወርዙቅኒ" ትርጉሙም: ‹‹አላህ ሆይ! ኃጢአቴን ማረኝ፤ እዘንልኝም፤ ድክመቴንም ጠግነኝ፤ ምራኝም፤ ሲሳይም ለግሰኝ፡፡››

42

ሱብሒ

43

ጁምዓህ

44

ሁለቱ ዒዶች

45

ዙህር

46

ዐስር

47

መግሪብ

48

ዒሻእ

49

“አት‐ተሒያቱ ሊላሂ ወስ‐ሶላዋቱ ወጥ‐ጠይ‐ዪባቱ፣ አስ‐ሰላሙ ዐለይከ አይዩሀን-ነቢይዩ ወረሕመቱልላሂ ወበረካትሁ፤ አስሰላሙ ዐለይና ወዓላ ዒባዲላሂ አስሷሊሒነ፣ አሽሀዱ አንላኢላሀ ኢልለልላህ ወአሽሀዱ አንነ ሙሐመደን ዐብዱሁ ወረሱሉሁ።” “ትርጉሙም: ክብርና ልዕልና እንዲሁም ሶላቶችና መልካም ነገሮች ሁሉ ለአላህ ናቸው። አንቱ ነቢዩ ሆይ! የአላህ ሰላም፣ እዝነቱና በረከቶች በእርሶ ላይ ይስፈን፤ ሰላም በእኛና በአላህ ደጋግ ባሮችም ላይ ይስፈን፤ ከአላህ ሌላ በእውነት የሚመለክ አምላክ እንደሌለ እመሰክራለሁ፤ ሙሐመድም የአላህ ባርያና መልዕክተኛው መሆናቸውንም እመሰክራለሁ።”

50

"አልላሁምመ ሰሊ ዐላ ሙሐመዲን ወዓላ ኣሊ ሙሐመዲን ከማ ሰለይተ ዐላ ኢብራሂም ወዐላ ኣሊ ኢብራሂም ወባሪክ ዓለ ሙሐመዲን ወዐላ አሊ ሙሐመዲን ከማ ባረክተ ዐላ ኢብራሂም ወዐላ ኣሊ ኢብራሂመ ኢነከ ሐሚዱን-መጂድ።" (ትርጉሙም፡ አላህ ሆይ! ሶለዋትህን በሙሐመድና በሙሐመድ ቤተሰብ ላይም አድርግ፤ ልክ በኢብራሂም እና በኢብራሂም ቤተሰቦች ሶለዋት እንዳደርግከው ሁሉ፤ አንተ ምስጉን የተከበርክ ነህና። አላህ ሆይ! በረከትህንም በሙሐመድ እና በመሐመድ ቤተሰቦች ላይም አድርግ ልክ በኢብራሂምና በኢብራሂም ቤተሰቦች እንዳደረግከው፤ አንተ ምስጉን የተከበርክ ነህና።)

51

ዙህር - ዐስር - መግሪብ - ዒሻእ

52

ሱብሒ - ጁሙዓህ - ሁለቱ ዒዶች

53

"አሏሁመ ሰሊ ዐላ ሙሐመዲን ወዓላ ኣሊ ሙሐመዲን ከማ ሰለይተ ዐላ ኢብራሂም ወዐላ ኣሊ ኢብራሂም ወባሪክ ዓለ ሙሐመዲን ወዐላ አሊ ሙሐመዲን ከማ ባረክተ ዐላ ኢብራሂም ወዐላ ኣሊ ኢብራሂመ ኢነከ ሐሚዱን-መጂድ።" (ትርጉሙም፡ አላህ ሆይ! ሶለዋትህን በሙሐመድና በሙሐመድ ቤተሰብ ላይም አድርግ፤ ልክ በኢብራሂም እና በኢብራሂም ቤተሰቦች ሶለዋት እንዳደርግከው ሁሉ፤ አንተ ምስጉን የተከበርክ ነህና። አላህ ሆይ! በረከትህንም በሙሐመድ እና በመሐመድ ቤተሰቦች ላይም አድርግ ልክ በኢብራሂምና በኢብራሂም ቤተሰቦች እንዳደረግከው፤ አንተ ምስጉን የተከበርክ ነህና።)

54

"አሰላሙ ዐለይኩም ወረሕመቱላህ" ትርጉሙም፦ የአላህ ሰላም እዝነት በእናንተ ላይ ይሁን ማለት ነው።

55

"በመጨረሻዋ ረከዓህ ላይ ሲቀመጥ የቀኝ እግሩን ተረከዝ ተክሎ የግራ እግሩን ተረከዝ ደግሞ በማሽሎክ መሬት ላይ ይቀመጣል" ቡኻሪይ ዘግበውታል።

56

"ተወሩክ" የተሰኘው አቀማመጥ

57

"አልላሁምመ ኢኒ አዑዙ ቢከ ሚን ዓዛቢ ጀሀነም፡ ወሚን ዓዛቢል ቀብር፡ ወሚን ፊትነቲል መሕያ ወልመማት፡ ወሚን ሸሪ ፊትነቲል መሲሒ ደጃል" ሙስሊም ዘግበውታል። ትርጉሙም: ‹‹አላህ ሆይ! ከጀሀነም ስቃይ፣ ከመቃብር ውስጥ ስቃይም፣ ከመኖርና ከመሞት ፈተናም፣ ከሐሳዊው መሲሕ (ከደጃል) ፈተናም በአንተ እጠበቃለሁ፡፡››

58

"አልላሁምመ ኢኒ ዘለምቱ ነፍሲ ዙልመን ከሢራ፡ ወላ የግፊሩ ዙኑበ ኢላ አንት፡ ፈግፊር ሊ መግፊረተን ሚን ዒንዲክ፡ ወርሓምኒ ኢነከ አንተል ገፉሩ ረሒም" ቡኻሪይ ዘግበውታል። ትርጉሙም: አላህ ሆይ! እኔ ነፍሴን በብዙ በድያለሁና ካንተም በስተቀር ኃጢአትን የሚምር ስለሌለ ካንተ ዘንድ የሆነ ምህረት አድርግልኝ፤ እዘንልኝም። አንተ በጣም መሃሪና አዛኝ ነህና።

59

"ሶስት ጊዜ አስተግፊሩሏህ" ማለት፤ ትርጉሙም፦ "አላህ ሆይ! መሀርታህን ለግሰኝ" ማለት ነው።

60

አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና ከአቡ ሁረይራ በተዘገበ ሐዲሥ የአላህ መልዕክተኛ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይሁን) እንዲህ ብለዋል፦ «የትኛውም ባርያ በእለተ ትንሳኤ መጀመርያ የሚተሳሰበው ሶላቱን ነው። በመሆኑም ሶላቱ ከተስተካከለች በርግጥ ድኗል ተሳክቶለታልም፤ እርሷ ከተበላሸች ደግሞ በርግጥ ተዋርዷል ከስሯልም።» አቡ ዳውድ፣ ቲርሚዚይ እና ነሳኢይ ዘግበውታል።