المختصر في صفة الحج

المختصر في صفة الحج

የሐጅ አፈፃፀም አጭር ማብራሪያ ምስጋና የአለማት ጌታ ለሆነው አላህ የተገባ ነው። ሶላትና ሰላም በነብያችን ሙሐመድ፣ በቤተሰቦቻቸውና በባልደረቦቻቸውም ላይ ሁሉ ይስፈን።

Language: lang_am
Prepared by: የእስላማዊ አስተምህሮቶችን በተለያዩ ቋንቋዎች አገልግሎት ማህበር የዕውቀት ዘርፍ ኮሚቴ
Version: 3.0
Translations 44
Amharic Assamese Azerbaijani Bambara +40
Attachments 7
PDF
Audio
Video
+3

የሐጅ አፈፃፀም አጭር ማብራሪያ ምስጋና የአለማት ጌታ ለሆነው አላህ የተገባ ነው። ሶላትና ሰላም በነብያችን ሙሐመድ፣ በቤተሰቦቻቸውና በባልደረቦቻቸውም ላይ ሁሉ ይስፈን።

ከዚህ በመቀጠል:-

ይህ የሐጅን አፈፃፀም የሚያብራራ አጠር ያለ መልዕክት ነው። አንድ ሐጅ አድራጊ በአብዛኛው ሊፈፅመው የሚገባውን ለማብራራት ጥረት አድርገናል።

ለተከበረው አላህ ጥርት ተደርጎ የተዘጋጀና ለአጠቃላይ ለሙስሊሙ ማህበረሰብም ጠቃሚ እንዲያደርግልን አላህን እንጠይቀዋለን።

የእስላማዊ አስተምህሮቶችን በተለያዩ ቋንቋዎች አገልግሎት ማህበር የዕውቀት ዘርፍ ኮሚቴ

መግቢያ

የመጀመሪያው: የአምልኮን ተቀባይነት የሚያስገኙ መስፈርቶች:

ሁለት መስፈርቶች እስካልተሟሉ ድረስ አምልኮ አላህ ዘንድ ተቀባይነት አይኖረውም።

እነርሱም:-የመጀመሪያው: ኢኽላስ (ስራን ፍፁም ለአላህ ብቻ ማድረግ): ይህም ስራው የአላህን ፊትና የመጪውን አለም ምንዳ ለማግኘት ታስቦ መሰራት አለበት። የበላይ የሆነው አላህ እንዲህ ብሏል: "አላህን ሃይማኖትን ለእርሱ ብቻ አጥሪዎች፤ ቀጥተኞች ሆነው ሊግገዙት እንጂ ያልታዘዙ ሲሆኑ (ተለያዩ)" [1] [አል-በይናህ፡ 5] የቁርአን አንቀፁ ትርጓሜ: ወደርሱና ወደ አምልኮው በመዞር ከርሱ ውጪ ያሉ አካላትን እንድትተዉ እንጂ ሌላ አልታዘዛችሁም ማለት ነው። ተፍሲር ሰዕዲይ (ገፅ 538)

ነቢዩም የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና እንዲህ ብለዋል:- "ሥራዎች (የሚለኩት) በኒያ ብቻ ነው። ሁሉም ሰው የሚያገኘው የነየተውን ነው።" (2) ቡኻሪ በቁጥር (1) እና ሙስሊም በቁጥር (1907) ዘግበውታል።

ሁለተኛው: በንግግርም ይሁን በተግባር ስራችን ነቢዩን የተከተለ መሆን አለበት። ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ ብለዋል: "በዚህ ጉዳያችን ከእርሱ ያልሆነን አዲስ መጤ ያመጣ ይዞት የመጣው አዲስ ፈሊጥ ውድቅ ነው።" ቡኻሪ በ(2697) ሙስሊም በ(1718) በሌላ የሙስሊም ዘገባ በ(1718) "በርሱ ላይ የኛ ትዕዛዝ የሌለበትን ነገር የሰራ ሰዉ ስራው ወደርሱ ተመላሽ ነዉ።" (3) ቡኻሪ በቁጥር (2697) እና ሙስሊም በቁጥር (1718) ዘግበውታል። (4) ሙስሊም በቁጥር (1718) ዘግበውታል።

***

የመጀመሪያው: የመዋቂት (የኢሕራም ማድረጊያ ጊዜና ስፍራዎች) ህግጋት:

መዋቂት (የኢሕራም ማድረጊያ ስፍራዎች): ማለት ሐጅ ወይም ዑምራ ማድረግ የፈለገ ሰው ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በርሳቸው ላይ ይስፈንና) ኢሕራም እንዲደረግበት የወሰኑዋቸው ስፍራዎች ናቸው።

ከነዚህ ስፍራዎች መካከል በአንዱ በኩል ሐጅን ወይም ዑምራን ነይቶ የሚያልፍ ሰው ከዛ ስፍራ ኢሕራም ማድረግ ግዴታው ነው። ያለ ኢሕራምም ያንን ስፍራ ማለፍ አይፈቀድለትም።

ከነዚህ ኢሕራም ማድረጊያ ስፍራዎች መካከል ወደ መካ ቅርብ የሆነ ሰው የርሱ ኢሕራም ማድረጊያ ስፍራው (ሚቃቱ) ያለበት ስፍራ ነው። ሐጅን ወይንም ዑምራን ኢሕራም የሚያደርገው ካለበት ስፍራ ሆኖ ነው።

የመካ ነዋሪዎችና በመካ የሚኖሩ ሰዎችም ለሐጅ ኢሕራም የሚያደርጉት ከመካ ነው። ለዑምራ ኢሕራም ማድረግ ከፈለጉ ግን ወደተንዒምና ወደ መሳሰሉት ከሐረም ክልል ውጪ ወደሆነ ስፍራ በመሄድ ነው ኢሕራም የሚያደርጉት።

በአየር የሚሄድ የሆነ ሰው በራሪው ኢሕራም በማድረጊያ ስፍራው (በሚቃቱ) ትይዩ ሲሆን ኢሕራም ያደርጋል። የኢሕራም ማድረጊያ ስፍራውን (ሚቃቱን) ትይዩ ከመሆኑ በፊትም ለኢሕራም ይዘጋጃል። እንዲሁም የኢሕራም ልብስንም ይለብሳል። በራሪው ከኢሕራም ማድረጊያ ስፍራ (ከሚቃቱ) ትይዩ ሲሆን ወዲያው ኢሕራም ያደርጋል። ከበራሪው እስኪወርድ ድረስ ሲጠብቅ ኢሕራሙን ማዘግየት አይፈቀድለትም። በራሪው ስለሚፈጥን ከኢሕራም ማድረጊያ ስፍራው ኢሕራም ሳያደርግ እንዳያልፍ ከሰጋ በራሪው ኢሕራም ማድረጊያ ስፍራውን ትይዩ ከመሆኑ በፊትም ለጥንቃቄ ያህል ተልቢያውን (ለበይከ አልላሁመ ለበይክ) መጀመር ይችላል።

ሁለተኛ: የሐጅ አፈፃፀም አይነቶች እና ህግጋታቸው:

የሐጅ አፈፃፀም አይነቶች ሶስት ናቸው። እነርሱም:- ተመቱዕ፣ ኢፍራድና ቂራን ናቸው።

ተመቱዕ እርድ ይዞ ላልመጣ ሰው በላጩ የሐጅ አፈፃፀም አይነት ነው። የተመቱዕ አፈፃፀምም: በሐጅ ወራት ውስጥ ዑምራን ኢሕራም ያደርጋል። ጦዋፍም አድርጎ በሶፋና መርዋ ከሮጠ በኋላ ከዑምራው ይፈታል። ከዚያም በዛው አመት ሐጅን ኢሕራም ማድረጉ ነው።

ኢፍራድ ማለት: ሐጅን ብቻ ኢሕራም ማድረግ ነው። መካ የገባ ጊዜም ጦዋፈል ቁዱም (መካ የመግባት ጦዋፍ) ማድረጉ ሱና ይሆንለታል። ከዚያም ለሐጅ ማድረግ የሚጠበቅበትን በሶፋና መርዋ ይሮጣል። ነገር ግን ፀጉሩን አይላጭምም አያሳጥርምም። ከኢሕራሙም አይፈታም። ይልቁንም የዒድ እለት ጀምረተል ዐቀባ ዘንድ ከወረወረ በኋላ ከኢሕራሙ እስኪፈታ ድረስ በኢሕራም ላይ እንዳለ ይቆያል። በሶፋና መርዋ መሮጥን ለሐጅ የሚያደርገውን ጦዋፍ (ጦዋፈል ኢፋዷ) ካደረገ በኋላ ለመሮጥ ማዘግየት ይችላል።

ቂራን: ዑምራንና ሐጅን ባጠቃላይ (ለበይከ አልላሁመ ዑምረተን ወሐጃ) በማለት አንድ ላይ አጣምሮ ኢሕራም ማድረግ ነው።

የቂራንን የሐጅ አፈፃፀም ኢሕራም ያደረገ ሰው የኢፍራድን የሐጅ አፈፃፀም ኢሕራም ያደረገ ሰው እንደሚሰራው ነው የሚሰራው፤ ነገር ግን የቂራንን ሐጅ አፈፃፀም ኢሕራም ያደረገ ሰው በርሱ ላይ እርድ ሲኖርበት የኢፍራድን የሐጅ አፈፃፀም ኢሕራም ያደረገ ሰው ግን እርድ የለበትም።

ሶስተኛ: የኢሕራም አፈፃፀም እና ህግጋቶቹ:

ኢሕራም ማድረግ ለፈለገ ሰው ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መፈፀሙ የተደነገገ ነው:

ገላ መታጠብ: ይህም ለወንድም ይሁን ለሴት የወር አበባና የወሊድ ደም ላይ ላለች ሴት ሳይቀር አፅንዖት የተሰጠው ሱና ነው።

- ከዑድ ቅባት ወይም ከሌላ ካገኘው ጥሩ መአዛ ካለው ቅባት ጭንቅላቱንና ፂሙን መቀባት። የተቀባው ቅባት ወይም ሽቶ ከኢሕራም በኋላም መቅረቱ ምንም ጉዳት የለውም። ሴት ከሆነች ግን ባዳ ወንዶች እንዳያሸቱት ሲባል ሽታ ያለውን ቅባት መቀባት አይፈቀድላትም።

- የኢሕራም ልብስ መልበስ: ይህም ሽርጥና ኩታ ነው። ነጫጭና ንፁህ ወይም አዳዲስ መሆናቸው ደሞ ሱና ነው። ሴት ልጅ ግን በጌጥ እስካልተጋለጠች ድረስ የፈለገችውን ልብስ ለብሳ ኢሕራም ታደርጋለች። ነገር ግን ኒቃብና ጓንት ከመልበስ ትቆጠባለች። ፊቷንና እጇንም ከነዚህ ውጪ ባለ ልብስ ትሸፍናለች።

ሶላቱ ግዴታም ይሁን ሱና የተደነገገ ከሆነ ሶላት በኋላ ኢሕራም ማድረግ፤ ይህ ግን ግዴታ አይደለም።

ዑምራ ከሆነ የሚያደርገው (ለበይከ አልላሁምመ ዑምረተን) የኢፍራድን የሐጅ አፈፃፀም ከሆነ የሚያደርገው (ለበይከ አልላሁምመ ሐጅጀን) የቂራንን የሐጅ አፈፃፀም ከሆነ የሚያደርገው ደግሞ (ለበይከ አልላሁምመ ዑምረተን ወሐጅጀን) ይበል።

ኢሕራም ማድረግ የፈለገ ሰው የሐጅ ወይም የዑምራ ስነ ስርዓቱን አሟልቶ ከመስራት የሚያደናቅፈኝ ነገር ይከሰታል ብሎ ከፈራ ኢሕራም ሲያደርግ (የሚያግደኝ ነገር ከተከሰተ የኢሕራሜ ፍፃሜ የታገድኩበት ቦታ ነው።) በማለት መስፈርት ማስቀመጥ ይፈቀድለታል። ኢሕራም ሲያደርግ ይህንን መስፈርት ካስቀመጠ በኋላ የሐጁን ወይም የዑምራውን ስነ ስርዓት ከመሙላት የሚያግደው ነገር ከተከሰተ በዛው ወቅት ከኢሕራሙ ይፈታል። ከዛ በኃላ የሚጠበቅበት ሌላ ግዴታ የለበትም።

ከዚያም ተልቢያ አብዝቶ ይበል: አፈፃፀሙም (ለበይከ አልላሁምመ ለበይከ፣ ለበይከ ላ ሸሪከ ለከ ለበይክ፣ ኢንነል ሐምደ ወንኒዕመተ ለከ ወልሙልክ ላ ሸሪከ ለክ) [2] ወንድ ከሆነ ተልቢያውን ሲል ድምፁን ከፍ ያደርጋል። ሴትም ብትሆን ባዳ ወንዶች ባሉበት ቦታ እስካልሆነች ድረስ ድምጿን ከፍ ታደርጋለች። ኢሕራም ላይ ያለ ሰው ተልቢያ ማብዛት ይገባዋል። በተለይ ሁኔታዎችና ወቅቶች ሲለዋወጡ ለምሳሌ ከፍታ ሲወጣ ወይም ቁልቁለት ሲወርድ ወይም ምሽት ወይም ንጋት ሲደርስ ተልቢያ አብዝቶ ይበል። [5] ሰውዬው (ለበይከ) ማለቱ ትርጉሙ: ጌታዬ ሆይ! ደግሜ ደጋግሜ ጥሪህን አቤት ብያለሁ። ሃሳቡም ሰውዬው የጌታውን ጥሪ ማክበሩንና ትእዛዙን ፈፃሚ መሆኑን እየገለፀ ነው። "ኢንነል ሐምደ ወንኒዕመተ ለከ ወልሙልክ" (ሐምድ) ማለት ተመስጋኝን ውዴታንና ልቅናን ባቀፈ ምሉዕ ባህሪያት ማሞገስ ማለት ነው። ደጋግሞ ካመሰገነ ውዳሴ ይባላል። (ወንኒዕመተ) ማለትም ባሮቹ ፍላጎታቸው እንዲሳካ እና የሚጎዳቸው እንዲወገድ ፀጋ የሚውልላቸው አላህ ነው። (አልሙልክ) ማለት ንግስናም ያንተ ነው። አላህ ተባረከ ወተዓላ ብቻ ነው ንጉሱ ማለት ነው። (ላ ሸሪከ ለክ) ማለት አላህ ብቸኛ በሆነበት ምሉዕ ባህሪያት አንድም የሚጋራው የለም ማለት ነው። አላህ ብቸኛ የሆነበትም ነገሮች ለምሳሌ ንግስና፣ መፍጠር፣ ማስተናበርና ተመላኪነት ይጠቀሳሉ። ከመጅሙዕ ፈታዋና ረሳኢሉል ዑሠይሚን (22/96) አጠር ተደርጎ የቀረበ።

ተልቢያ ማድረግ የዑምራ አፈፃፀም ላይ ከሆነ ኢሕራም ካደረገበት ወቅት ጀምሮ ጦዋፍ ማድረግ እስኪጀምርበት ድረስ፤ የሐጅ አፈፃፀም ላይ ከሆነ ደግሞ ኢሕራም ካደረገበት ወቅት ጀምሮ የዒድ እለት ጀምረተል ዐቀባን መወርወር እስኪጀምርበት ጊዜ ድረስ ማለቱ የተደነገገ ነው።

አንድ ኢሕራም ያደረገ ሰው ከኢሕራሙ እስኪፈታ ድረስ ሙሕሪም የሚከለከላቸው ነገሮችን ከመዳፈር መጠንቀቅ ግዴታው ነው።

አራተኛ: ኢሕራም ላይ ክልክል የሆኑ ነገሮች

ኢሕራም ላይ ክልክል የሆኑ ነገሮች የሚከተሉት ናቸው:

- ሰውነቱ ላይ የሚገኝን ማንኛውንም ፀጉር መላጨት ወይም ማሳጠር፤

- የእግርንም ይሁን የእጅ ጥፍርን ሙሉ ለሙሉም ይሁን የተወሰነውን መቁረጥ፤

- ከጭንቅላት ጋር የሚነካካ በሆነ ነገር ጭንቅላትን መሸፈን፤ ለምሳሌ: ኮፊያና ጥምጣም፣ ኩታን ወይም መሀረብ ጭንቅላት ላይ ማኖር ወይም ብርድልብስ ወይም ካርቶንና ከነዚህ ውጪም መሰል ነገሮችን ለጭንቅላት መሸፈኛ የሚታሰቡ ነገሮችን ጭንቅላት ላይ ማድረግ ነው። ይህ ክልከላ ግን ሴቶችን ሳይሆን ወንዶችን ብቻ ነው የሚመለከተው።

- የተለመደውን በሰውነት ልክ ተለክተው የሚዘጋጁ ልብሶችን በተለመደው መልኩ መልበስ ነው፤ ለምሳሌ ያህል የተሰፉ ሙሉ ልብሶች፣ ሱሪ፣ ጀለቢያ፣ ካልሲ፣ ጓንት ይጠቀሳሉ። ይህ ግን ሴቶችን ሳይሆን ወንዶችን ብቻ የሚመለከት ነው። ሴት ልጅ የምትከለከው:-

- ኒቃብ ወይም ማንኛውም ኒቃብን የመሰሉ ፊት መሸፈኛዎችን መልበስ ነው፤ ባዳ ወንዶች ፊት ግን መሸፈኛው ከፊቷ ጋር ቢነካካ እንኳ በተለመደው ፊት መሸፈኛ ፊቷን የመሸፈን ግዴታ አለባት። ፊቷን ስትሸፍን ከፊቷ ጋር እንዳይነካካ በሚል ማሰሪያ ነገር ወይም የመሳሰሉትን ማኖር አይደነገግላትም። ይህ የተደነገገ መሆኑን የሚጠቁምም ምንም ማስረጃ የለም።

- እጆቿ ላይ ጓንቶችን ማጥለቅም ትከለከላለች፤ ባዳ ወንዶች ፊት ግን እጆቿን ዓባያዋ ውስጥ በመክተት የመሸፈን ግዴታ አለባት።

- ሰውነቱን ወይም የኢሕራም ልብሱን ሽቶ መቀባት፤

- የየብስ እንስሶችን አድኖ መግደል ወይም ባይገድሉ እንኳን የማደን ሙከራ ማድረግ፤

- ለራሱም ይሁን ለሌላ ሰው ማጨት፤

- ኒካሕ ማሰር፤

- ከግንኙነት ውጪ ያለ የስሜት መነካካትም ለምሳሌ መሳምና በስሜት መተሻሸት፤

- ግብረ ስጋ ግንኙነት ማድረግ፤

***

አምስተኛ: የጠዋፍ አፈፃፀም

ኢሕራም ያደረገ ሰው መስጂደል ሐራም ሲገባ ቀኝ እግሩን ማስቀደሙ ሱና ነው። መስጂድ ሲገባ የሚባለውን ዱዓም ይበል። መስጂድ ሲገባ ከሚባሉ ዱዓዎች መካከል እጅግ የተረጋገጠው ዱዓ "አልላሁመ-ፍተሕ ሊ አብዋበ ረሕመቲክ" ትርጉሙም "አላህ ሆይ! የእዝነት በርህን ክፈትልኝ" ማለት ነው። ይህን ዱዓ የሚለውም መስጂደል ሐራም ሲገባ ብቻ ሳይሆን ማንኛውም መስጂድ ሲገባ ነው።

ጠዋፍ መጀመር የፈለገ ጊዜ "የኢድጢባዕ" አለባበስ ይለብሳል። አለባበሱም: የኩታውን መሃል ቀኝ ብብቱ ስር በመክተት የኩታውን ጫፎች በግራ ትከሻው ላይ ማድረግ ነው። ጦዋፍ አድርጎ እንደጨረሰም ኩታውን ከጦዋፍ በፊት ወደነበረበት አለባበስ ይመልሰዋል። የኢድጢባዕ አለባበስ የሚፈፀመው በጦዋፍ ወቅት ብቻ ነው።

ቀጥሎ ወደ ሐጀረል አስወድ (ጥቁሩ ድንጋይ) ቀደም በማለት በቀኝ እጁ ጥቁሩን ድንጋይ በመዳበስ ይስመዋል፤ መሳሙ ካልገራለት በእጁ ይዳብስና እጁን ይሳም፤ ይህም ካልገራለት በእጁ ሰላም ይለዋል ወይም እንደ ዘንግና የመሳሰሉት ነገር በመዳበስ ይስመዋል። ይህም ካልገራለት ወደ ሐጀረል አስወድ በመዞር እጁን ወደርሷ በመጠቆም እጁን ሳይስም ያልፋል። በላጩ ምንም ሳይገፋፋ ሰዎችን ሳያውክና በሰዎች ሳይታወክ መፈፀም ነው።

ጥቁሩን ድንጋይ ሲዳብስ ወይም ወደርሱ ሲጠቁም (አላሁ አክበር) ይበል።

ከዚያም ቀኝ አቅጣጫን በመያዝ በይተል ሐራምን በግራው በኩል ያደርጋል። ሩክነል የማኒ ጋር ሲደርስ ሳይስመው ይዳብሰዋል። ይህም ካልገራለት ምንም ሳይገፋፋም በእጁም ወደርሱ ሳይጠቁም ያልፋል።

በሩክነል የማኒ እና ሐጀረል አስወድ መካከል ሲደርስ (ረብበና አቲና ፊ ዱንያ ሐሰነተን ወፊልአኺረቲ ሐሰነተን ወቂና ዓዛበን-ናር) ይበል። ትርጉሙም (ጌታችን ሆይ! በምድረ አለም ደግን ነገር (ፀጋን) በመጨረሻይቱም አገር ደግን ነገር (ገነትን) ስጠን፤ የእሳትንም ቅጣት ጠብቀን።) ማለት ነው።

በሐጀረል አስወድ በኩል ባለፈ ቁጥር በእጁ ወደርሱ በመጠቆም (አላሁ አክበር) ይላል።

በተቀሩት የጠዋፍ ዙሮች የፈለገውን ዚክር፣ ከዱዓና ቁርአን ይበል።

ሱናው በሶስቱ የመጀመሪያ ዙሮች ሶምሶማ ማድረግ ነው። ሶምሶማ ማለት: እርምጃዎችን ከማቀራረብ ጋር ፈጠን ያለ አረማመድ መራመድ ነው። የተቀሩትን አራት ዙሮች ግን የተለመደውን እርምጃ እንጂ የሚራመደው ሶምሶማ አያደርግም።

ጦዋፉን አሟልቶ እንደጨረሰ ወደ መቃም ኢብራሂም በመሄድ ይህንን ይላል: (ወትተኺዙ ሚን መቃሚ ኢብራሂመ ሙሶላ) ትርጉሙም (ከኢብራሂምም መቆሚያ መስገጃን አድርጉ።) ማለት ነው። (አል‐በቀራህ: 125) ቀጥሎ ከገራለት ሁለት ረከዓን ከመቃሙ ኢብራሂም ኋላ ይሰግዳል። ካልገራለት ደግሞ መስጂዱ ውስጥ በሚገኝ ማንኛውም ስፍራ ይሰግዳል። በመጀመሪያው ረከዓ ከፋቲሓ በኋላ: በላቸው «እናንተ ከሓዲዎች ሆይ!» [ሱረቱ አል-ካፊሩን:1] በሁለተኛው ረከዓ ከፋቲሓ በኋላ {በል «እርሱ አላህ አንድ ነው፡፡ } [አልኢኽላስ:1]

ስድስተኛ: የሰዕይ (የመሮጥ) አፈፃፀም:

ከጦዋፍና ከሁለቱ ረከዓዎች ያጠናቀቀ ጊዜ ወደ መሮጫ ስፍራ ይወጣል። ወደ ሶፋ የቀረበ ጊዜ ይህንን ይላል: (ኢንነስ-ሰፋ ወልመርወተ ሚን ሸዓኢሪልለሏህ) ትርጉሙም (ሰፋና መርዋ ከአላህ (ትእዛዝ መፈፀሚያ) ምልክቶች ናቸው። ) ማለት ነው። ከዚያም "አላህ ከጀመረበት እጀምራለሁ።" ይላል። (ሰፋና መርዋ ከአላህ /ትዕዛዝ መፈጸሚያ/ ምልክቶች ናቸው... ) ቀጥሎም እንዲህ ይበል: ከዚያም "አብደኡ ቢማ በደአ'ላሁ ቢሂ" (ትርጉሙ፡ አላህ ከጀመረበት እጀምራለሁ።) [6] (6) ሙስሊም በቁጥር (1218) ዘግበውታል።

ቀጥሎ ካዕባን መመልከት እስኪችል ወይም ወደ ካዕባ አቅጣጫ ዞሮ ካዕባን እስከሚቅጣጭ ድረስ ወደ ሰፋ ይወጣል። እንዲህ በማለት አላህን በመነጠል ተክቢራ ይላል፡ (ላ ኢላሃ ኢለላህ ወሕደሁ ላ ሸሪከ ለህ፤ ለሁል ሙልኩ ወለሁል ሐምዱ ወሁወ ዐላ ኩሊ ሸይኢን ቀዲር፤ ላ ኢላሃ ኢለላሁ ወሕደህ፣ አንጀዘ ወዕደህ፣ ወነሰረ ዐብደህ፣ ወሀዘመል አሕዛበ ወሕደህ) (ትርጉሙም፡ ከአላህ በቀር በእውነት የሚመለክ አምላክ የለም፤ ለርሱም ተጋሪ የለውም፤ ንግሥናም የርሱ ብቻ ነው፤ ምስጋናም ለርሱ ብቻ የተገባው ነው፤ እርሱ በሁሉም ነገር ላይ ቻይ ነው፤ ከአላህ በቀር በእውነት የሚመለክ አምላክ የለም፤ ብቸኛ አምላክ ነው፤ ቃሉንም ፈፀመ፤ ባርያውንም ድልን አቀዳጀ፤ ብቻውን ሆኖ ስብስቦችን አሸነፈ።) የሚለውን ውዳሴ ሶስት ጊዜ ደጋግሞ ይበል። በየመሃሉም ዱዓ ያድርግ። (ላ ኢላሃ ኢለላህ ወሕደሁ ላ ሸሪከ ለህ፤ ለሁል ሙልኩ ወለሁል ሐምዱ ወሁወ ዐላ ኩሊ ሸይኢን ቀዲር፤ ላ ኢላሃ ኢለላሁ ወሕደህ፣ አንጀዘ ወዕደህ፣ ወነሶረ ዐብደህ፣ ወሀዘመል አሕዛበ ወሕደህ) (ትርጉሙም፡ ከአላህ በቀር በእውነት የሚመለክ አምላክ የለም፤ ለርሱም ተጋሪ የለውም፤ ንግሥናም የርሱ ብቻ ነው፤ ምስጋናም ለርሱ ብቻ የተገባው ነው፤ እርሱ በሁሉም ነገር ላይ ቻይ ነው፤ ከአላህ በቀር በእውነት የሚመለክ አምላክ የለም፤ ብቸኛ አምላክ ነው፤ ቃሉንም ፈፀመ፤ ባርያውንም ድልን አቀዳጀ፤ ብቻውን ሆኖ ስብስቦችን አሸነፈ።) ከዚያም በዚህ መካከል የቻለውን ያህል ዱዓእ ያደርጋል (አላህን ይማጸናል)። ይህንን ዚክር እና ዱዓእ ደግሞ ሶስት ጊዜ ደጋግሞ ይላል። [7] (7) ሙስሊም በቁጥር (1218) ዘግበውታል።

ቀጥሎም ከሰፋ ወደ መርዋ እየተራመደ ይወርዳል። አረንጓዴው ምልክት ዘንድ ሲደርስም በደንብ ይሮጣል። ሁለተኛው አረንጓዴ ምልክት ዘንድ ሲደርስ ደሞ የተለመደ እርምጃውን ይራመድ። ለሴት ልጅ በደንብ መሮጥ አልተደነገገም።

መርዋ ዘንድ የደረሰ ጊዜ ሰፋ ላይ የፈፀመውን (ሁለተኛው አንቀፅ ላይ ቀደም ብሎ የተጠቀሰውን) አምሳያ ማድረግ ተደንግጎለታል።

ከዚያም ከሶፋ ወደ መርዋ እየተራመደ ይወርዳል። አረንጓዴው ምልክት ዘንድ ሲደርስም በደንብ ይሮጣል። ሁለተኛው አረንጓዴ ምልክት ዘንድ ሲደርስ ደሞ የተለመደ እርምጃውን ይራመድ።

ሰባት ዙር እስኪሞላ ድረስም በዚሁ መልኩ ይፈፅማል። ከሶፋ ተነስቶ መርዋ እስኪደርስ ያለው ጉዞ አንድ ዙር ይባላል። ከመርዋ ወደ ሶፋ ሲመለስ ደግሞ ሁለተኛ ዙር ይባላል።

እየሮጠ ሳለም የፈለገውን ዚክር፣ ዱዓና ቁርአን ይበል።

ሰባተኛ: ፀጉርን የመላጨትና የማሳጠር አፈፃፀም

ዑምራ አድራጊው ጦዋፉንና መሮጡን እንዳሟላ ወንድ ከሆነ ጭንቅላቱን መላጨቱ ወይም ማሳጠሩ ግዴታ ነው። ሱናው መላ የጭንቅላትን ፀጉር መላጨት ወይም ማሳጠር ነው።

ዑምራው የተፈፀመው እስከ ሐጅ ድረስ ባለው ጊዜ የጭንቅላት ፀጉር ድጋሚ በማይበቅልበት ለሐጅ ወቅት ትንሽ ሲቀረው በሆነበት ወቅት ካልሆነ በቀር መላጨት ከማሳጠር በላጭ ነው። ለሐጅ ትንሽ ሲቀረው ከሆነ ግን በማሳጠር ላይ ብቻ ይቆጠብ።

ዑምራ አድራጊዋ ሴት ከሆነች ከፀጉሯ ጫፍ የጣት ክፋይ ያህል ታሳጥር።

በኢፍራድም ይሁን ወይም በቂራን ሐጅን ኢሕራም ያደረገ ሰው የዒድ እለት ጀምረተል ዐቀባ ዘንድ ከወረወረ በኋላ እንጂ ፀጉሩን አይቁረጥ።

ዑምራ አድራጊና የተመቱዕ ሐጅን ኢሕራም ያደረገ ሰው የዑምራውን አምልኮ በዚህ ያጠናቅቃል።

የሐጅ አፈፃፀም

የመጀመሪያው: ሐጅን ኢሕራም ማድረግ:

ሐጅ ማድረግ ለፈለገ ሰው ሱናው የተርዊያ ቀን ማለትም የዙልሒጃ ስምንተኛው ቀን ረፋድ ላይ ሐጅ ማድረግ ካሰበበት ቦታ ኢሕራም ማድረጉ ነው። መካ ውስጥ ወይም ከሚቃት (ኢሕራም ማድረጊያ ክልል) በታች ከሆነ ካለበት ስፍራ ኢሕራም ያደርጋል። ያለበለዚያ ከሚያልፍበት ሚቃት (ኢሕራም ማድረጊያ ክልል) ኢሕራም ያደርጋል።

ለዑምራ ኢሕራም ሲየደርግ የሰራውን አምሳያ እንደ ገላ መታጠብ፣ ሽቶ መቀባት፣ ሶላት መስገድና የመሳሰሉትን ሐጅን ኢሕራም ሲያደርግም ይፈፅማል። ለሐጅ ኢሕራም ማድረግን በመነየት ተልቢያ ያደርጋል። ሐጅ ላይ የሚያደርገው ተልቢያ ለዑምራ ከሚያደርገው ተልቢያ ጋር ተመሳሳይ ነው። ነገር ግን ለሐጅ ተልቢያ ሲል (ለበይከ ዑምራህ) ከሚለው ፋንታ (ለበይከ ሐጀን) ነው የሚለው።

ኢሕራም ማድረግ የፈለገ ሰው የሐጅ ወይም የዑምራ ስነ ስርዓቱን አሟልቶ ከመስራት የሚያደናቅፈኝ ነገር ይከሰታል ብሎ ከፈራ ኢሕራም ሲያደርግ (የሚያግደኝ ነገር ከተከሰተ የኢሕራሜ ፍፃሜ የታገድኩበት ቦታ ነው) በማለት መስፈርት ማስቀመጥ ይፈቀድለታል። ኢሕራም ሲያደርግ ይህንን መስፈርት ካስቀመጠ በኋላ የሐጁን ወይም የዑምራውን ስነ ስርዓት ከመሙላት የሚያግደው ነገር ከተከሰተ በዛው ወቅት ከኢሕራሙ ይፈታል። ምንም የማድረግ ግዴታም አይኖርበትም።

ከዚያም ተልቢያ አብዝቶ ይበል: አፈፃፀሙም (ለበይከ አልላሁምመ ለበይከ፣ ለበይከ ላ ሸሪከ ለከ ለበይክ፣ ኢንነል ሐምደ ወንኒዕመተ ለከ ወልሙልከ ላ ሸሪከ ለክ) ወንድ ከሆነ ተልቢያውን ሲል ድምፁን ከፍ ያደርጋል። ሴትም ብትሆን ባዳ ወንዶች ባሉበት ቦታ እስካልሆነች ድረስ ድምጿን ከፍ ታደርጋለች። ኢሕራም ላይ ያለ ሰው ተልቢያ ማብዛት ይገባዋል። በተለይ ሁኔታዎችና ወቅቶች ሲለዋወጡ ለምሳሌ ከፍታ ሲወጣ ወይም ቁልቁለት ሲወርድ ወይም ምሽት ወይም ንጋት ሲደርስ ተልቢያ አብዝቶ ይበል።

ተልቢያን ማለት ከኢሕራም ጀምሮ የዒድ እለት ጀምረተል ዐቀባ ዘንድ መወርወር እስኪጀምር ድረስ የተደነገገ ነው።

አንድ ኢሕራም ያደረገ ሰው ከኢሕራሙ እስኪፈታ ድረስ ሙሕሪም የሚከለከላቸውን ነገሮች ከመዳፈር መጠንቀቅ ግዴታው ነው።

***

ሁለተኛ: በሚና ማደር:

ቀጥሎ በስምንተኛ ቀን ወደ ሚና መሄዱ ሱና ነው። በሚናም ዙህርን፣ ዐስርን፣ መግሪብን፣ ዒሻንና ፈጅርን (ባለአራት ረከዓዎቹን ወደ ሁለት ረከዓ) እያሳጠረ ሳይሰበስብ ይሰግዳል። ይህም ነቢዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ሚና ላይ ሳይሰበስቡ አሳጥረው ይሰግዱ ስለነበር ነው።

ሶስተኛ: የዐረፋ ምድር ላይ መቆምና ሙዝደሊፋ ማደር:

የዐረፋ ቀን የዘጠነኛው ቀን ፀሐይ ስትወጣ ከሚና ወደ ዐረፋ ይጓዛል። ፀሐይ ወደ መግቢያዋ እስክትዘነበልም ድረስ ከገራለት ወደ ነሚራ ወርዶ ያሳልፋል። ያለበለዚያ ግን ወደ ነሚራ ባይወርድም ችግር የለውም። ወደ ነሚራ መውረድ ሱና ነው።

ፀሐይ ወደ መግቢያዋ ስትዘነበልም ዙህርና ዐስርን ሁለት ሁለት ረከዓ ይሰግዳል። ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንደፈፀሙት ሁለቱንም በአንድ ወቅት ጀምዑ ተቅዲም አድርጎ (ማለትም በዝሁር ወቅት) ሰብስቦ ይሰግዳቸዋል።

በመቀጠል ሶላት ከሰገደ በኋላ ዚክርና ዱዓ በማድረግ፣ ወደ አላህ ዐዘ ወጀል በመዋደቅ ይጠመዳል። ወደ ቂብላ በመዞርም እጁን ከፍ አድርጎ ዱዓ ያደርጋል።

በዚህ ታላቅ ስፍራ በቆሙ ወቅት አብዛኛው የነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በርሳቸው ላይ ይስፈንና) ዱዓ "ላኢላሃ ኢለሏሁ ወሕደሁ ላሸሪከ ለህ፤ ለሁል ሙልኩ ወለሁል ሐምዱ ወሁወ ዐላ ኩሊ ሸይኢን ቀዲር" (ትርጉሙ፡ ከአላህ በስተቀር በእውነት የሚመለክ አምላክ የለም፤ ብቸኛ ነው ለእርሱ ምንም ተጋሪ የለውም፤ ንግስና ሁሉ ለእርሱ ነው፤ ምስጋናም ሁሉ ለእርሱ ነው፤ እርሱ በሁሉ ነገር ላይ ቻይ ነው) የሚለው ነበር።

ድካም ከተሰማውና ከጓደኞቹ ጋር ጠቃሚ ወሬዎችን በማውራት ማረፍ ከፈለገ ወይም የገራለትን ጠቃሚ መጽሐፍትን ማንበብ ከፈለገ በተለይ በዛን ቀን በአላህ ላይ ያለው ተስፋ እንዲጠነክር የአላህን ቸርነትና የስጦታውን ታላቅነት የሚገልፁ መጽሐፍትን ማንበቡ ይመረጣል። ቀጥሎ በዱዓው ወደ አላህ ወደመዋደቁ ይመለሳል። የቀኑን የመጨረሻ ክፍል በዱዓ ለመጠቀም ጥረት ያድርግ። ምርጡ ዱዓ የዐረፋ ቀን ዱዓ ነውና።

የዐረፋ ቀን ፀሐይ ስትጠልቅም ወደ ሙዝደሊፋ ይጓዝ።

ሙዝደሊፋ ሲደርስም መግሪብን ሶስት ረከዓ ዒሻን ደግሞ ሁለት ረከዓ አድርጎ በአንድ ወቅት ሰብስቦ ይሰግዳቸዋል።

እኩለ ሌሊት ከሆነ በኋላ ካልሆነ በቀር ሙዝደሊፋ አልደርስም ብሎ ከፈራ ሙዝደሊፋ ባይደርስም እንኳ ባለበት ቦታ ይሰግዳቸዋል። ሶላቱን ከእኩለ ሌሊት በኋላ አዘግይቶ መስገድ አይፈቀድለትም።

ሙዝደሊፋ ያድራል። ጎህ መውጣቱን ሲያረጋግጥ ፈጅርን አዛንና ኢቃም ብሎ በጊዜ ይሰግዳል።

ከዚያም በደንብ ወገግ እስኪል ድረስ መሽዓረል ሐራም ዘንድ አላህን እየነጠለና እያላቀ እንዲሁም የፈለገውን ዱዓ እያደረገ ያሳልፋል። ወደ መሽዓረል ሐራም መሄድ ካልገራለት ባለበት ቦታ ሆኖ ዱዓ ያደርጋል። ይህም ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ ስላሉ ነው፡ "እኔ እዚህ ቆሜያለሁ። ጀምዕ (ሙዝደሊፋ) ባጠቃላይ መቆሚያ ነው።" ዚክርና ዱዓ በሚያደርግበት ወቅት ወደ ቂብላ ዞሮና እጆቹን ከፍ አድርጎ መሆን አለበት። "እኔ እዚህ ቆሜያለሁ። ጀምዕ (ሙዝደሊፋ) ባጠቃላይ መቆሚያ ቦታ ነው።" [8] ዚክርና ዱዓ በሚያደርግበት ወቅት ወደ ቂብላ ዞሮና እጆቹን ከፍ አድርጎ መሆን አለበት። [8] አቡ ዳውድ በቁጥር (1936) ላይ ዘግበውታል።

አራተኛ: የዒድ እለት ሥራዎች:

ንጋቱ በጣም ወገግ ያለ ጊዜ ፀሐይ ከመውጣቱ በፊት ከሙዝደሊፋ ወደ ሚና ይመለሳል። ዋዲ ሙሐስሲር ሲደርስ ፍጥነቱን ይጨምራል።

ሚና የደረሰ ጊዜም ጀምረተል ዐቀባ ዘንድ አንድ በአንድ እያደረገ አከታትሎ ሰባት ጠጠር ይወረውራል። እያንዳንዱ ጠጠርም የተምር ፍሬ ያህል የሚጠጋ መጠን ያለው መሆን አለበት። ከየሁሉም ውርወራ ጋርም ተክቢራ ይበል። ጀምረተል ዓቀባ መካን ቀጥላ ያለቸውና የመጨረሻዋ መወርወሪያ ናት።

ቀጥሎ ከገራለት እርዱን ይረድ።

ቀጥሎ ወንድ ከሆነ ይላጭ ወይም ያሳጥር። መላጨቱ ግን በላጭ ነው። ሴት ከሆነች ደሞ ለርሷ የተደነገገላት መላጨት ሳይሆን ማሳጠር ነው።

ከወረወረና ከተላጨ የመጀመሪያውን ከሐጅ ኢሕራም መፈታት ተፈቷል ወይም አጠናቋል። ግንኙነት ከመፈፀም ውጪ ቀደም ብሎ የተከለከለው ሁሉ ይፈቀድለታል።

ቀጥሎ ወደ መካ በመውረድ ጠዋፈል ኢፋዷን ጠዋፍ ያደርጋል። ቀጥሎ ኢሕራም ያደረገው የተመቱዕን የሐጅ አፈፃፀም ከሆነ የሐጁን መሮጥ በሰፋና መርዋ መካከል ይሮጣል። የኢፍራድን ወይም የቂራንን የሐጅ አፈፃፀም ከሆነ ኢሕራም ያደረገው የመግቢያ ጠዋፍ (ጠዋፈል ቁዱም) ካደረገ በኋላ በሰፋና መርዋ መካከል ካልሮጠ ከጠዋፈል ኢፋዷ በኋላ ይሮጣል። ጠዋፉንና መሮጡን እስከምሽት ድረስ ወይም እስከሁለተኛ ቀን ድረስ እንደተመቸው ማዘግየት ይችላል።

አምስተኛ: የአያመ ተሽሪቅ ተግባራት

ከወረወረ፣ ከተላጨ፣ ጠዋፍ ካደረገና ከሮጠ ከሁሉም የኢሕራም ክልከላዎች ተፈቷል። ግንኙነት እንኳ ሳይቀር ሁሉም ነገርም ይፈቀድለታል።

ወደ ሚና በመመለስ የዙልሒጃን አስራ አንደኛና አስራ ሁለተኛ ቀን ምሽቶችን እዛው ያድራል። እዛው ሆኖ ከዘገየ ደግሞ የአስራ ሶስተኛውን ምሽትም እዛው ያድራል።

ፀሐይ ወደ መግቢያዋ ስትዘነበልም በሶስቱም ጠጠር መወርወሪያ ውስጥ ጠጠሮችን ይወረውራል።

በአስራ አንደኛው ቀን የመጀመሪያው ጠጠር መወርወሪያ ጋር ሰባት ጠጠሮችን አከታትሎ አንድ በአንድ ይወረውራል። በየሁሉም ውርወራም ተክቢራ ይላል። (ይህ ከመካ እጅግ የራቀውና ወደ መስጂድ ኸይፍ ደግሞ ቅርብ የሆነው መወርወሪያ ቦታ ነው።) ቀጥሎ ትንሽ ቀደም ይልና የፈለገውን ዱዓ ረዘም ላለ ወቅት ያደርጋል። ረዘም ላለ ወቅት ዱዓ ማድረግና መቆም ከከበደው ሱናው እንዲገኝለት ያህል የገራለትን ቀለል አርጎ ዱዓ ያደርጋል።

ቀጥሎ በዚሁ መልኩ መካከለኛው ጠጠር መወርወሪያ ዘንድ ይወረውራል። ከርሷ በኋላም ዱዓ ያደርጋል።

ቀጥሎ ጀምረተል ዐቀባ ዘንድ በዚሁ መልኩ ይወረውራል። ነገር ግን ጀምረተል ዐቀባ ዘንድ ወርውሮ እንዳጠናቀቀ ዱዓ ሳያደርግ ይሄዳል።

ቀጥሎ በአስራ ሁለተኛ ቀንም ልክ እንደ አስራ አንደኛ ቀን ጠጠሮችን ይወረውራል። ጠጠሮችን ወርውሮ እንዳጠናቀቀ ከፈለገ በፍጥነት ከሚና ለቆ ይሄዳል።

ከፈለገ ደግሞ ቆይቶ እዛው ሚና የአስራ ሶስተኛ ምሽትን አድሮ ቀደም ብሎ በተጠቀሰው መልኩ ፀሐይ ወደ መግቢያዋ ከተዘነበለች በኋላ ሶስቱንም መወርወሪያ ዘንድ ይወረውራል። መዘግየቱ በላጭ ነው።

ሚና እያለ የአስራ ሁለተኛ ቀን ፀሃይ የጠለቀች ካልሆነ በቀር ወደ አስራ ሶስተኛ ቀን መዘግየቱ ግዴታ አይደለም። ሚና እያለ የአስራ ሁለተኛ ቀን ፀሐይ ከገባች ግን የአስራ ሶስተኛ ቀን ፀሐይ ወደ መግቢያዋ እስክትዘነበል ድረስ ጠብቆ ሶስቱ ጠጠር መወርወሪያዎች ዘንድ እስኪወረውር የመዘግየት ግዴታ ይኖርበታል።

ነገር ግን ሳይፈልግ የአስራ ሁለተኛ ቀን ፀሐይ ሚና እያለ ብትገባ ለምሳሌ ጓዙን ጠቅልሎ ወጥቶ በትራፊክ መጨናነቅና በመሳሰሉት እዛው ሚና እያለ ፀሐይ ብትገባበት የማደር ግዴታ አይኖርበትም። ምክንያቱም ፀሐይ እስክትገባ ድረስ የዘገየው ያለምርጫው ነውና።

ስድስተኛ: ጦዋፈል ወዳዕ (የመሰናበቻ ጦዋፍ)

ከመካ ወደ ሃገሩ መመለስ የፈለገ ጊዜ ጦዋፈል ወዳዕ ሳያደርግ አይወጣም።

ነገር ግን የወር አበባና የወሊድ ደም እያየች ያለች ሴት የመሰናበቻ ጦዋፍ ማድረግ አይጠበቅባትም። ከነቢዩ (ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም) የመጣ ነገር ስለሌለ ለመሰናበት የመስጂደል ሐራም በሩ ጋር መቆምም አይገባቸውም።

ወደ ጉዞ መውጣት የፈለገ ጊዜም የመጨረሻ ተግባሩን በአላህ ቤት ጦዋፈል ወዳዕ ማድረግ ይሁን።

ከጠዋፈል ወዳዕ በኋላ ጓደኞቹን ለመጠበቅ ወይም ሻንጣውን ለመጫን ወይም ለመንገዱ የሚያስፈልገውን ለመግዛት ከቀረ ችግር የለውም። ከጉዞ መዘግየትን እስካልነየተ ድረስ ጦዋፉን አይደግመውም። ለምሳሌ የቀኑ መጀመሪያ ላይ ሊጓዝ ፈልጎ ጦዋፈል ወዳዕን አደረገ። ቀጥሎ ለምሳሌ ጉዞውን ወደ ቀኑ መጨረሻ ቢያዘገይ የመጨረሻ ተግባሩ የአላህን ቤት መሰናበት እንዲሆን ጦዋፉን መድገም ይጠበቅበታል።

***