الأذكار التي تقال صباحًا ومساءً

الأذكار التي تقال صباحًا ومساءً

الأذكار التي تقال صباحًا ومساءً كتبها بخط يده فضيلة الشيخ العلامة محمد بن صالح العثيمين من صحيح الأذكار الثابتة عن النبي -صلى الله عليه وسلم-

Language: lang_am
Prepared by:
Version: 2.0
Translations 56
Amharic Assamese Azerbaijani Bengali +52
Attachments 7
PDF
Audio
Video
+3

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡ ጧትና ማታ የሚባሉ ዚክሮች

(አላህ ከእርሱ በቀር ሌላ አምላክ የለም፡፡ ሕያው ራሱን ቻይ ነው፡፡ ማንገላጀትም እንቅልፍም አትይዘውም፡፡ በሰማያት ውስጥና በምድር ውስጥ ያለው ሁሉ የርሱ ብቻ ነው፡፡ ያ እርሱ ዘንድ በፈቃዱ ቢሆን እንጅ የሚያማልድ ማነው? (ከፍጡሮች) በፊታቸው ያለውንና ከኋላቸው ያለውን ሁሉ ያውቃል፡፡ በሻውም ነገር እንጂ ከዕውቀቱ በምንም ነገር አያካብቡም (አያውቁም)፡፡ መንበሩ ሰማያትንና ምድርን ሰፋ፡፡ ጥበቃቸውም አያቅተውም፡፡ እርሱም የሁሉ በላይ ታላቅ ነው፡፡) (አያቱል ኩርሲይ አል በቀራህ፡ 255)

(መልክተኛው ከጌታው ወደ ርሱ በተወረደው አመነ፡፡ ምእምኖቹም (እንደዚሁ)፡፡ ሁሉም በአላህ፣ በመላዕክቱም፣ በመጻሕፍቱም፣ በመልክተኞቹም ከመልክተኞቹ «በአንድም መካከል አንለይም» (የሚሉ ሲሆኑ) አመኑ፡፡ «ሰማን፤ ታዘዝንም፡፡ ጌታችን ሆይ! ምሕረትህን (እንሻለን)፡፡ መመለሻም ወዳንተ ብቻ ነው» አሉም። * አላህ ነፍስን ከችሎታዋ በላይ አያስገድዳትም፡፡ ለርስዋ የሠራችው አላት፡፡ በርስዋም ላይ ያፈራችው (ኀጢአት) አለባት፡፡ (በሉ)፡- ጌታችን ሆይ! ብንረሳ ወይም ብንስት አትያዘን፤ (አትቅጣን)፡፡ ጌታችን ሆይ! ከባድ ሸክምን ከእኛ በፊት በነበሩት ላይ እንደጫንከው በእኛ ላይ አትጫንብን፡፡ ጌታችን ሆይ! ለኛም በርሱ ችሎታ የሌለንን ነገር አታሸክመን፡፡ ከእኛም ይቅርታ አድርግ ለእኛም ምሕረት አድርግ፡፡ እዘንልንም፤ ዋቢያችን አንተ ነህና፡፡ በከሓዲዎች ሕዝቦች ላይም እርዳን፡፡) (አል በቀራህ 285 - 286)

(በል «እርሱ አላህ አንድ ነው፡፡) (በል «በተፈልቃቂው ጎህ ጌታ እጠበቃለሁ፡፡) (በል «በሰዎች ፈጣሪ እጠበቃለሁ፡፡) ሙሉ ምዕራፉን (አል'ኢኽላስን፣ አል'ፈለቅን እና አንናስን) ሦስት ጊዜ ይነበባሉ።

«አዑዙ ቢከሊማቲላሂ አትታማቲ ሚን ሸሪ ማ ኸለቀ» (ምሉዕ በሆኑት የአላህ ቃላት ከፈጠራቸው ነገሮች ክፋት እጠበቃለሁ።) (ሦስት ጊዜ) ይባላል።

«ቢስሚላሂ ለዚ ላ የዹሩ መዐ_ስሚሂ ሸይኡን ፊል አርዺ ወላ ፊ ስሰማኢ ወሁወ አስ'ሰሚዑል ዐሊም።» (በዚያ ከስሙ ጋር በምድርም ይሁን በሰማይ ምንም ነገር የማይጎዳ በሆነው እንዲሁም ሰሚና ዐዋቂ በሆነው አላህ ስም።) (ሦስት ጊዜ) ይባላል።

«ረዺቱ ቢልላሂ ረበን ወቢል ኢስላሚ ዲነን ወቢ ሙሐመዲን ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ነቢየን» (የአላህን ጌትነት ፣ የእስልምናን ሃይማኖትነት፣ የሙሐመድን (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ነብይነት ወደድኩ (ተቀበልኩ)።) (ሦስት ጊዜ) ይባላል።

«አስበሕና ወአስበሐል ሙልኩ ሊላሂ፤ ወልሐምዱ ሊላሂ፤ ላኢላሃ ኢለላሁ ወሕደሁ ላሸሪከ ለሁ፤ ለሁል ሙልኩ ወለሁል ሐምዱ ወሁወ ዐላ ኩልሊ ሸይኢን ቀዲር፤ ረብቢ አስአሉከ ኸይረ ማ ፊ ሀዘል የውሚ ወኸይረ ማ በዕደሁ፤ ወአዑዙ ቢከ ሚን ሸርሪ ማ ፊ ሀዘል የውሚ ወሚን ሸሪ ማ በዕደሁ፤ ረብቢ አዑዙ ቢከ ሚነል ከሰሊ ወል ሀረሚ ወሱኢል ኪበር፤ ወአዑዙ ቢከ ሚን ዐዛቢ አንናሪ ወዐዛቢል ቀብር።» (እኛም አነጋን፤ ንግስናም የአላህ ሆኖ አነጋ። ምስጋና ለአላህ የተገባ ነው። ከአላህ ውጭ (በእውነት) የሚመለክ አምላክ የለም ፤ ብቸኛና አጋር የሌለው ነው ፤ ንግስና እና ምስጋና ለርሱ ነው ፤ እርሱ በሁሉም ነገር ላይ ቻይ ነው። ጌታዬ ሆይ! በዚህ ቀን ውስጥም ከዚህ ቀንም በኋላ ያለን መልካም ነገር እጠይቅሃለሁ። በዚህ ቀን ውስጥም ከዚህ ቀንም በኋላ ካለው ክፉ ነገርም በአንተ እጠበቃለሁ። ጌታዬ ሆይ! ከስንፍና ፣ ከመጃጀትና ከመጥፎ እርጅና በአንተ እጠበቃለሁ። ጌታዬ ሆይ! ከእሳት ቅጣት እና ከቀብር ቅጣት በአንተ እጠበቃለሁ።) ምሽት ላይ ደግሞ እንዲህ ይላል፦ እኛም ንግስናም የአላህ ሆነን አመሸን። … እንዲህም ይላል፦ (ጌታዬ ሆይ የዚህንም ሌሊት እና ከዚህ ሌሊት በኋላም ያለን መልካም ነገር እማፀንሀለሁ... እስከመጨረሻው አዝካር ድረስ፡ (እኛም ንግስናም የአላህ ሆኖ አነጋን።) እና (በዚህ ቀን ውስጥ) በሚለው ፈንታ።

«አልላሁምመ ቢከ አስበሕና ወቢከ አምሰይና ወቢከ ነሕያ ወቢከ ነሙቱ ወኢለይከ_ንኑሹር።» (ጌታዬ ሆይ! በአንተ (ጥበቃ) አነጋን ፤ በአንተ (ጥበቃም) አመሸን ፤ በአንተ (ስም) ህያው እንሆናለን ፤ በአንተ (ስምም) እንሞታለን ፤ መቀስቀስም ወደ አንተ ብቻ ነው።) ምሽት ላይ ደግሞ እንዲህ ይላል፦ «አልላሁምመ ቢከ አምሰይና ወቢከ አስበሕና ወቢከ ነሙቱ ወቢከ ነሕያ ወኢለይከል መሲር።» (ጌታዬ ሆይ! በአንተ (ጥበቃ) አመሸን በአንተ (ጥበቃም) አነጋን ፤ በአንተ (ስም) ህያው እንሆናለን በአንተ (ስም) እንሞታለን። መመለሻም ወደ አንተ ብቻ ነው።)

«አልላሁምመ ማ አስበሐ ቢ ሚን ኒዕመቲን አው ቢአሐዲን ሚን ኸልቂከ ፈሚንከ ወሕደከ ላ ሸሪከ ለከ ፈለከል ሐምዱ ወለከ አሽሹክሩ።» (አላህ ሆይ! በኔ ወይም ከፍጡራንህ በአንዱ ላይ ያነጋው ፀጋ ከአንተው ብቻና ብቻ ነው። ለአንተ አጋር የለህም ምስጋናና ውዳሴም ይገባሀል። ምሽት ላይ ደግሞ እንዲህ ይላል፦ (በኔ ላይ ያነጋው በሚለው ፈንታ) በኔ ላይ ያመሸው።

(ሦስት ጊዜ።)

«አልላሁምመ ኢንኒ አስአሉከል ዓፊየተ ፊድዱኒያ ወል አኺረቲ፤ አልላሁምመ ኢንኒ አስአሉከል ዐፍወ ወል ዓፊየተ ፊ ዲኒ ወዱንያየ ወአህሊ ወማሊ፤ አልላሁምመ ስቱር ዐውራቲ ወአሚን ረውዓቲ፤ አልላሁምመ ኢሕፈዝኒ ሚን በይኒ የደይየ ወሚን ኸልፊ ወዐን የሚኒ ወዐን ሺማሊ ወሚን ፈውቂ፤ ወአዑዙ ቢዐዞመቲከ አን ኡጝታለ ሚን ተሕቲ።» (አላህ ሆይ! በዚህችም ሆነ በቀጣዩ ዓለም ጤናን እጠይቅሀለሁ። አላህ ሆይ! በዚህችም ሆነ በቀጣዩ ዓለም በሃይማኖቴ እና በቅርቢቱ ዓለም ህይወቴ በቤተሰቦቼም በንብረቴም ይቅርታህንና ጤናን እጠይቅሃለሁ። አላህ ሆይ! ነውሬን ሸፍንልኝ። ለስጋቴ (ለፍርሃቴ) ደህንነትን ለግሰኝ። አላህ ሆይ! ከፊት ለፊቴ ከኋላዬም ከበስተቀኜም ከበሰተግራዬም ከበላዬም ጠብቀኝ። ከበታቼም እንዳልጠቃ በልቅናህ እጠበቃለሁ።)

«አልላሁምመ አንተ ረቢ ላኢላሀ ኢልላ አንተ ኸለቅተኒ ወአነ ዐብዱከ ወአነ ዐላ ዐህዲከ ወወዕዲከ መስተጠዕቱ፤ አዑዙ ቢከ ሚን ሸሪ ማሰነዕቱ፤ አቡኡ ለከ ቢኒዕመቲከ ዓለይየ፤ ወአቡኡ ቢዘንቢ፤ ፈግፊር ሊ ፈኢነሁ ላ የግፊሩ አዝ‐ዙኑበ ኢልላ አንተ።» (አላህ ሆይ! አንተ ጌታዬ ነህ። ከአንተ በስተቀር ሌላ በእውነት የሚመለክ አምላክ የለም። ፈጥረኸኛል። እኔም ባርያህ ነኝ። ላንተ የገባሁትን ቃል ኪዳን ለመሙላት የቻልኩትን ያህል እጥራለሁ። (የገባህልኝንም) ቀጠሮ አምናለሁ። ከሰራሁት ነገር ክፋት በአንተ እጠበቃለሁ።በኔ ላይ ለዋልከው ፀጋም እውቅናን እሰጣለሁ። ኃጢአት መስራቴንም አምናለሁ። ምህረትህን ለግሰኝ። እነሆ ካንተ በስተቀር ኃጢአትን የሚምር ማንም የለምና።)

«አልላሁምመ ፋጢረስ_ ሰማዋቲ ወል አርዲ፤ ዐሊመል ገይቢ ወሽ_ሸሃደቲ፤ ረብበ ኩሊ ሸይኢን ወመሊከሁ፤ አሽሀዱ አን ላኢላሀ ኢልላ አንተ፤ አዑዙ ቢከ ሚን ሸርሪ ነፍሲ ወሚን ሸርሪሽ_ሸይጧኒ ወሺርኪሂ ወአን አቅተሪፈ ዐላ ነፍሲ ሱአን አው አጁረሁ ኢላ ሙስሊም።» (የሰማያትና የምድሩ ፈጣሪ የሆንከው፣ የሩቁን እና የቅርቡን አዋቂ ፤ የሁሉም ነገር ጌታ እና ባለቤት የሆንከው አላህ ሆይ! ከአንተ በስተቀር ሌላ በእውነት የሚመለክ አምላክ አለመኖሩን እመሰክራለሁ። ከነፍሴ ተንኮል እንዲሁም ከሸይጧን ተንኮል እና የሽርክ ጥሪው (ውትወታው)፣ በነፍሴ ላይ መጥፎ ከመስራትም ይሁን ሙስሊም በሆነ ሰው ላይ መጥፎን ከመፈፀም በአንተ እጠበቃለሁ።)

«አልላሁምመ ኢንኒ አስበሕቱ ኡሽሂዱከ ወኡሽሂዱ ሐመለተ ዐርሺከ ወመላኢከቲከ ወአንቢያአከ ወጀሚዐ ኸልቂከ ቢአንነከ አንተ አልላሁ ላ ኢላሀ ኢልላ አንተ ወአንነ ሙሐመደን ዐብዱከ ወረሱሉከ» (አላህ ሆይ! አንተ አምላክ መሆንህን ከአንተ በስተቀርም በእውነት የሚመለክ አምላክ አለመኖሩን እና ሙሐመድም ባርያህና መልዕክተኛህ መሆናቸውን አንተን፣ የዐርሽህን ተሸካሚዎች፣ መላእክትህን፣ አንቢያኦችህን (ነብያቶችህን) እንዲሁም ሁሉንም ፍጡራኖችህን ምስክር አድርጌ አነጋሁ።) በምሽት ደግሞ «አሏሁመ ኢኒ አምሰይቱ» ( ... አስመስክሬ አመሸሁ።) እስከመጨረሻው (አራት ጊዜ)።

«ላኢላሀ ኢለላሁ ወሕደሁ ላ ሸሪከ ለሁ ለሁል ሙልኩ ወለሁል ሐምዱ ወሁወ ዐላ ኩሊ ሸይኢን ቀዲር።» (ከአላህ ውጭ በእውነት የሚመለክ አምላክ የለም። ተጋሪም የለውም። ንግስናም ምስጋናም የሚገባው ለእርሱ ብቻ ነው። እርሱ በነገሮች ላይ ሁሉ ቻይ ነው።) (መቶ ጊዜ) ንጋት ወይም ምሽት ላይ።

«ሐስቢየልላሁ ላ ኢላሀ ኢላ ሁው፤ ዐለይሂ ተወከልቱ፤ ወሁወ ረቡል ዐርሺል ዐዚም።» (አላህ በቂዬ ነው፤ ከእርሱ በቀር ሌላ በእውነት የሚመለክ የለም፤ በእርሱ ተመካሁ፤ እርሱም የታላቁ ዐርሽ ጌታ ነው።) (ሰባት ጊዜ)

«ሱብሓነ'ላሂ ወቢሐምዲሂ።» (ጥራት እና ምስጋና ለአላህ ተገባው።) (መቶ ጊዜ) ሲነጋ እና ሲመሽ። ወይም በሁለቱም ወቅት።

«አስተግፊሩላሀ ወአቱቡ ኢለይሂ» (አላህን ምህረቱን እጠይቀዋለሁ፤ ወደ እርሱም በፀፀት እመለሳለሁ።) (መቶ ጊዜ።)

ለመጻፍ የገራልኝ ይህን ያክል ነው፤ ሌሎች የሚጠቀሙበት እንዲያደርገው አላህን እማጸነዋለሁ።

ጸሐፊ ሙሐመድ አስ'ሷሊሕ አል'ዑሠይሚን (አላህ ይዘንላቸው) ቀን 20-1-1418 ሂ