زيارة غار حراء

زيارة غار حراء

የሒራን ዋሻ መዘየር

Language: lang_am
Prepared by: በልዩ ልዩ ቋንቋዎች የኢስላማዊ ይዘት አገልግሎት ማህበር የሊቃውንት ኮሚቴ
Version: 1.0
Translations 11
Amharic Bengali English Persian +7
Attachments 7
PDF
Audio
Video
+3

የሒራን ዋሻ መዘየር

በልዩ ልዩ ቋንቋዎች የኢስላማዊ ይዘት አገልግሎት ማህበር የሊቃውንት ኮሚቴ

የሒራ ዋሻ የሚገኘው ከመካ ሰሜን ምስራቅ በኑር ተራራ ጫፍ ላይ ነው። የተራራው ከፍታም 634 ሜትር ይደርሳል ተብሎ ይገመታል።

ዋሻው እጅግ ጠባብ ከመሆኑ የተነሳ ከ3 ሰው በላይ ማስቀመጥ አይችልም።

የተከበሩት ነቢያችን ሙሐመድ (ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም) ነቢይ ተደርገው ከመላካቸው በፊት የተወሰኑ ቀናቶችን በተለይም በረመዷን ወር ውስጥ ስለአላህ የሰማያትና የምድር መለኮታዊነት ለማስተንተንና ለማስተዋል ከሰዎች ርቀው ብቻቸውን በዚህ ዋሻ ውስጥ ያሳልፉ ነበር። እሳቸው ዘንድም ብቸኝነት ተወዳጅ ሆኖ ነበር።

ይህ ስፍራ ከሚለይባቸው ዋና ዋና ነገሮች መካከል:

ተራራው ለመውጣት የሚከብድና አዳጋች አቀበታማ መንገድ በመሆኑ ዋሻውም ከሰዎች ጫጫታና መበጥበጥ የራቀ ነው። ነው። ከካዕባም 2 ኪሎ ሜትር አካባቢ ይርቃል። ዋሻው ቀደም ብሎ በስተምዕራብ በኩል ክፍተት ነበረው። በዛም ክፍተት የተከበረው ከዕባ ይታይ ነበር። ይህም ለማስተንተንና ለማስተዋል የሚጋብዝ ነው።

የተከበሩት ነቢይ (ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም) ተልዕኳቸውን የጀመሩትም ከዚህ ጭር ካለ ስፍራና ከዚህ አስቸጋሪ ተራራ ከፍታ ላይ ነው። እዚሁ ሳሉም ነበር የመጀመሪያው የቁርአን አንቀፆች በሳቸው ላይ የወረዱት፡ {አንብብ በዚያ (ሁሉን) በፈጠረው ጌታህ ስም። 1} [አልዐለቅ: 1]

ከዚያም ወደ ኸዲጃ - አላህ መልካም ስራዋን ይውደድላትና - ባዩት አስደንጋጭ ነገር ፈርተውና ደንግጠው እንዲህ እያሉ ተመለሱ፡ "አከናንቡኝ አከናንቡኝ።" [1] እስከ ዕለተ ትንሳኤ ድረስ የአላህ ሰላትና ሰላም በርሳቸው፣ በቤተሰቦቻቸውና በባልደረቦቻቸው ላይ ይስፈንና።

(የሒራን ዋሻ ለመጎብኘት ያሰብክ) ሙስሊም ወንድሜ ወይም ያሰብሽ ሙስሊማ እህቴ ሆይ! [1] ቡኻሪ በኪታብ አትተፍሲር በቁጥር (4642)፣ ሙስሊም በኪታብ አልአይማን ወደ አላህ መልክተኛ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም የወሕይ አጀማመር በሚለው ምዕራፍ በቁጥር (160) ዘግበውታል።

በሁሉም ሁኔታዎቻችንና ጉዳዮቻችን የርሳቸውን ስብዕና ተምሳሌት አድርገን እንድንተገብረው ሙስሊም የሆነ ሰው የነቢዩን (ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም) ታሪክ ማወቁና ማጥናቱ ወሳኝ ጉዳይ ነው። ነገር ግን እኛንም እነርሱንም አላህ ይምራንና አንዳንድ ጎብኚዎች የሚፈፅሙት ነቢዩ (ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም) ካስተማሩት ቀጥተኛና ቀና ጎዳና ተፃራሪ የሆኑ ጉዳዮች ከእስልምና አስተምህሮት ውስጥ የሌለና ንፁሁ ሸሪዓም ያልመጣበት ጉዳይ ከመሆኑም ባሻገር ጉዳዩ ክልከላን ያስተናገደ ርዕስ ነው። ለምሳሌ:- በድንጋይ ሰውነትን እንደሚተሻሹት፣ በዛፎች በረከትን መፈለግ ወይም ድንጋዩን መሳምና መላስ ወይም ከዚህ ውጪ ያሉ ውግዝ ተግባራት ለአብነት ይጠቀሳሉ።

ከነዚህ መካከል አንዱን እንኳ ቢሆን መልክተኛው (ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም) ተግብረዋል? ወይስ አዘውታልን? ወይስ ከርሳቸው ህልፈት በኋላ የተከበሩት ሶሓቦቻቸው አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና ተግብረውታልን? በፍፁም! አንድ ሺህ ጊዜ በፍፁም! ከነዚህ ሁሉ የባሰው ወንጀል ደግሞ እነዚያ ከአላህ ዐዘ ወጀል ውጪ እርዳታን የሚጠይቁ ናቸው። ነቢዩ (ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም) ለኢብኑ ዐባስ አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና ሲመክሩት እንዲህ ብለውታል: "አንተ ልጅ ሆይ! የአላህን ትእዛዝና ክልከላ ጠብቅ አላህ ይጠብቅሃል። የአላህን ትእዛዝና ክልከላ ጠብቅ ከፊትህ ታገኘዋለህ። ማንኛውንም ነገር ስትለምን ከአላህ ዘንድ ለምን፤ እርዳታ ከፈለግክም በአላህ ታገዝ። ...." [2]

ለዚህም ሲባል በኛ ላይ ባጠቃላይ ለነርሱ ምክር መለገስና በነርሱ ላይ ማውገዝ ግዴታችን ነው። ይህም ነቢዩ (ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ ስላሉ ነው: "ከእናንተ መካከል መጥፎ ሢሠራ የተመለከተ፥ በእጁ ይለውጠው (ያስተካክለው)፤ ይህንን ካልቻለ በምላሱ ይከላከል፤ ይህንንም ካልቻለ በቀልቡ (ልቡ) ይጥላ ይህ ግን ደካማው የኢማን ክፍል ነው።" ሙስሊም ዘግበውታል። [3] [2] ቲርሚዚይ ስለ ቂያማ ሁኔታ፣ ልብን ስለሚያለሰልሱና ስለ ጥንቁቅነት በዘገቡባቸው ምዕራፎች ውስጥ በሐዲሥ ቁጥር (2516) ዘግበውታል። አሕመድም በሙስነድ ዑሥማን ቢን ዐፋን በሐዲሥ ቁጥር (2763) ዘግበውታል።

ይህ አንድ ሙስሊም በሌላው ሙስሊም ላይ ካሉት መብቶች መካከል አንዱ ነው። እንዲሁም አንድ ባሪያ ልዕለ ኋያሉ ጌታችን አሏህ እንዲህ በማለት በሱረቱል ዐስር ያዘዘውን ትእዛዝ መተግበርም ነው: {እነዚያ ያመኑትና መልካሞችን የሠሩት፣ በእውነትም አደራ የተባባሉት፣ በመታገስም አደራ የተባባሉት ብቻ ሲቀሩ፡፡ 3} [አል ዐስር: 3] [3] ሙስሊም በኪታብ አልኢማን "ከመጥፎ መከልከል ከኢማን እንደሆነ፣ ኢማን እንደሚጨምርና እንደሚቀንስ፣ በጥሩ ማዘዝና ከመጥፎ መከልከል ግዴታዎች እንደሆኑ ለመግለፅ የመጣ" በሚለው ምዕራፍ በሐዲሥ ቁጥር (49) ዘግበውታል።

አንዳንድ ሰዎች ለሐጅ ወይም ለዑምራ ወይም ከዛ ውጪ ለሆነ ጉዞ በወጡበት የሒራእን ዋሻ ለመጎብኘት አስበው የሚሄዱና ወደ አላህ የሚያቃርባቸው መስሏቸውም በአስቸጋሪው መንገድ በመጓዝ ራሳቸውን በማጨናነቅ ነፍሳቸው የሚያደክሙ አሉ። ጉዳዩ ግን እንደሚያስቡት አይደለም። ይልቁንም እንዲህ አይነቱ ድርጊት ለአላህ ትእዛዝም ሆነ መቃረቢያ ባልሆነ ነገር ራስን ማድከም ነው። ከዛም አልፎ አላህ የከለከለውን ክልከላ ውስጥ መግባትም ነው።

ከነዚህም መካከል የተወሰኑት አላህ ይምራቸውና የአላህ መልክተኛ (ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም) ይዘውት የመጡትን የተውሒድ ጥሪ የሚፃረሩ የተወሰኑ ተግባራትን ይፈፅማሉ ወይም የኢማንን ምሉዕነት የሚያጎድፉ መጤ ቢድዓዎችን ይተገብራሉ።

የአላህ መልክተኛ (ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም) ወደርሳቸው ከሰማይ ወሕይ ከመውረዱ በፊት በሒራ ዋሻ አላህን ይገዙ የነበረ ቢሆንም ወሕይ በርሳቸው ላይ ተከታትሎ ከወረደ በኋላ ግን የሒራእን ዋሻ ለዱዓም ሆነ ለሶላት ወይም ከዛ ውጪ ላለ አምልኮ አስበውት አያውቁም።

የሒራእንም ዋሻ ሆነ የተወሰኑ ሰዎች ዛሬ ላይ መዘየሩ ይወደዳል ወደ አላህም ያቃርባል ብለው የሚሞግቷቸውን ስፍራዎችን ነቢዩ (ሶለሏሁ ዓለይሂ ወሰለም) መካ ውስጥ 13 ዓመት ገደማ ሲቆዩ ለአምልኮ ማሰባቸው አልተዘገበም።

በመካ ውስጥ አምልኮ፣ ሶላትና ዱዓ ለመፈፀም አስበን የምንሄደው ብቸኛው ልዩ ስፍራ መስጂደል ሐራም ብቻ ነው።

ሌሎች በሐጅ ወቅት ሐጅ አድራጊው የሚጓዝባቸው የሐጅ ማድረጊያ ስፍራዎች ራሱ ዓረፋ፣ ሚናና ሙዝደሊፋ ሁሉም ሙስሊም በታወቁት የሐጅ ወቅት ካልሆነ በቀር ወደነዚህ ስፍራ አምልኮን ለመፈፀም አስቦ መሄዱ አልተደነገገለትም። ይህም በተለዩ ቀናት ሳይዘገይም ሆነ ሳይቀድም አላህ በደነገገው መልኩ ብቻ እንጂ ከዛ ውጪ የአምልኮ ማድረጊያ ልዩ ስፍራ አይደሉም። በሐዲሥ እንደተረጋገጠው (መካ ውስጥ) በማንኛውም ወቅት ያለምንም ገደብ አምልኮ ለመፈፀም የሚጓዙበት ልዩ ስፍራ መስጂደል ሐራም ብቻ ነው። "እናንተ በኒ ዓብድ መናፍ ሆይ! በማንኛውም በፈለገው የምሽቱም ሆነ የቀኑ ክፍለ ጊዜ በዚህ ቤት ጦዋፍ ማድረግና መስገድ የፈለገን ሰው እንዳትከለክሉ።" አስሓቡ ሱነን ዘግበውታል። [4]

የተከበርከው ሙስሊም ወንድሜ ሆይ! ሶስቱ የሐጅ መተግበሪያ ስፍራዎች ዓረፋ፣ ሚና፣ ሙዝደሊፋና ጠጠር መወርወሪያዎቹ ስፍራዎች አላህ ከኢብራሂም ዓለይሂ ሰላም ዘመን ጀምሮ የደነገጋቸው - በአንዳንድ ዘገባዎች ከአደም ዘመን ጀምሮ የደነገጋቸው - በተገደበ ወቅትና በተለየ ሁኔታ አምልኮ የሚፈፀምባቸው ተብለው የተለዩ ስፍራዎች ከሆኑ ታዲያ ሰዎች ሌሎችን ስፍራዎች ለአምልኮ መተግበሪያነትና ለመቃረቢያ አስበው መፈብረካቸው እንዴት ሊፈቀድላቸው ይችላል? እንዴትስ ለአምልኮ መተግበሪያነት የፈበረኩትን ስፍራ ለፈለገ ሰው በሁሉም ጊዜ በማንኛውም ወቅት ለአምልኮ መተግበሪያነት ማዋል ይፈቀድላቸዋል? ለምሳሌ የሒራእ ዋሻና ሌሎችም [4] ቲርሚዚይ በሐጅ ምዕራፎች በ"ከዐስርና ከሱብሒ በኋላ ጦዋፍ ያደረገ ሰው ስለ መስገዱ" በሚለው ምዕራፍ ስር በሐዲሥ ቁጥር (868) ዘግበውታል፤ ነሳኢይ በኪታቡል መዋቂት በ"በመካ ውስጥ በሁሉም ሰአት ሶላት መስገድ መፈቀዱ" በሚለው ምዕራፍ ስር በሐዲሥ ቁጥር (585) ዘግበውታል።

ነቢዩ (ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም) ከተሰደዱም በኋላ በተለያዩ ጊዜያት ወደ መካ የመጡ ቢሆንም ነገር ግን በፍፁም የሒራ ዋሻ ዘንድ አልመጡም። የተደነገገና መቃረቢያ አምልኮ ቢሆን ኖሮ ወደ ሒራ ይመጡ ነበር። ከማንም በላይ እሳቸው ወደ ሒራ ለመምጣት የተገቡ ሰው ናቸው። ምክንያቱም ከነቢይነት በፊት አምልኮ መፈፀሚያ ስፍራቸው ስለነበር ከሳቸው በፊትም ሆነ በኋላ ለማንም የሌለው ትዝታ እሳቸው ከሒራ ዋሻ ጋር ትልቅ ትዝታ አላቸውና።

እንደሚታወቀው ነቢዩ (ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም) ከመሰናበቻው ሐጃቸው ጋር አራተኛውን ዑምራቸውን አድርገዋል። ከርሳቸው ጋርም በርካታ ሙስሊሞች አብረዋቸው አድርገዋል። አላህ የሻበት ካልሆነ በቀር ከርሳቸው ጋር አብሮ ሐጅ ከማድረግ የቀረ የለም። እርሳቸው በነዚህ ጉዟቸው ሁሉ ከሶሓቦቻቸውም አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና ወደ ሒራ ዋሻ የወጣም ሆነ የዘየረ አንድም የለም። መካ ዙሪያ ወደሚገኝ ወደ አንድም ስፍራ አልሄዱምም። በመስጂደል ሐራም፣ በሶፋና መርዋ መካከል፣ በሚና፣ በሙዝደሊፋና በዓረፋ ካልሆነ በቀር አንድም አምልኮ የተፈፀመበት ሌላ ስፍራ አልነበረም። ቀጥሎም ከአራቱ ቅን ምትኮችና ከሌሎችም ቀዳሚ ሶሓቦች ህልፈት በኋላ ወደ ሒራ ዋሻና ወደመሳሰሉት ስፍራ ለሶላት፣ ዱዓ ለማድረግና በረከትን ለመፈለግ የሚሄዱ አልነበሩም።

ይህ የተደነገገና አላህም የሚመነዳበት ተወዳጅ ስራ ቢሆን ኖሮ ከርሳቸው በኋላ ከመጡት ሰዎች ይልቅ ነቢዩ (ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም) ከሰዎች ሁሉ በበለጠ ባወቁትና በከጀሉት ነበር። አንዱንም ከነዚህ መካከል አለመስራታቸው በዲንና በሸሪዓ የተከለከለው አዲስ መጤ መሆኑን ያስረዳናል። ከዚህ በኋላ ያመፀና አምልኮና መቃረቢያ ያደረገው ሰው ከነቢዩ (ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም) እና ከሶሓቦች ውጪ የሆነን መንገድ ተከትሏል። አላህ ያልፈቀደውንም አምልኮ ደንግጓል። አላህ ሱብሓነህ እንዲህ ብሏል: {ለእናንተ አላህንና የመጨረሻውን ቀን የሚከጅል ለሆነ ሰው፣ አላህንም በብዙ ለሚያወሳ በአላህ መልዕክተኛ መልካም መከተል አልላችሁ፡፡} [አልአሕዛብ: 21]